የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ108 ሺህ እስከ 305 ሺህ ያለአግባብ የወሰዱትን ገንዘብ " እስካሁን አልመለሱልኝም " ያላቸውን ግለሰቦች ፎቶግራፍ ይፋ አደረገ። ወደዚህ እርምጃ ከመግባቱ በፊት በተደጋጋሚ ማስጠንቀቁን አስታውሷል። በዚሁ መሠረት እስካሁን ያላግባብ የወሰዱትን ገንዘብ ያልመለሱ ግለሰቦችን የመጀመሪያ ዙር ፎቶግራፍ ይፋ ማድረጉን ገልጿል። አሁንም ለመጨረሻ ጊዜ እስከ መጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም የተራዘመውን የገንዘብ መመላሽ ዕድል ተጠቅመው ገንዘብ ያልመለሱ እንዲመልሱ አስጠንቅቋል። በተሰጠው የጊዜ ገደብ የማይመልሱትን ወደ ህግ እንደሚያቀርብም ገልጿል። https://combanketh.et/list-of-customers/?fbclid=IwAR2ZWAndWBR1lt_ytwfDL9IiTYrml76PgdWo_FBhLxRRMTF01VxzN1ekfKA 16.7K views19:33