ቻይና፤ አሜሪካ ጸብ አጫሪ ድርጊት ከፈጸመች ምላሽ ለመስጠት መዘጋጀቷን ገለጸች ፤ አሜሪካ ከዚህ በኋላ ጸብ አጫሪ ድርጊት ከፈጸመች ምላሽ ለመስጠት መዘጋጀቷን የቻይና ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታወቀ፡፡
የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ በሰጠው መግለጫ ዋሸንግተን በቻይና ብሔራዊ ጥቅም ላይ ያነጣጠረ ጸብ አጫሪ ድርጊት ከፈጸመች እንደማይታገስ ገልጿል፡፡ የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ዋንግ ዌንቢን ዛሬ በመግለጫቸው አሜሪካ፤ ቻይናን ለመያዝ ታይዋንን ከመጠቀም እንድትቆጠብ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል፡፡