በቃልህ ሰውን አትግደል ! በአንድ ብርዳማ የክረምት ለሊት ንጉሱ ከጉዞው ወደ ቤቱ ይመለሳል ፣ በደጃፉም ላይ ከጠባቂዎቹ አንዱ ሽማግሌ ብርዱን ሊቋቋም ማይችል ልብስ ለብሰው ቆመዋል ፣ ንጉሱም ወደሳቸው ተጠጋና .... "ለመሆኑ በዚህ ብርድ ይሄን ለብሰህ ትቋቋማለህ? " ሲል ጠየቃቸው ። " እውነት ነው በጣም ይበርዳል ግን ደግሞ የክረምቱን ብርድ ማሳልፍበት ልብስ ስለሌለኝ ችለዋለሁ ! " ብሎ መለሰለት ። ንጉሱም .... " አሁን ውስጥ እንደገባሁ አንዱን አገልጋይ ብርዱን ምትከላከልበት ልብስ ይዞልህ እንዲመጣ ልክልሀለው " ሲለው በጣም ተደሰተ ። ይሁንና ንጉሱ ወደ ውስጥ ሲገባ ሽማግሌውን ረሳው ፣ ወደራሱ ጉዳዮች ገባ ። ንጉሱ ጠዋት ሲወጣ ሽማግሌው መሬት ላይ ተደፍቶ አጠገቡ አንዲት ወረቀት ላይ ... " ንጉስ ሆይ የገደለኝ ቃልህ እንጂ ብርዱ አደለም ፣ ብርዱንማ ሁሌም እቋቋመው ነበር ዛሬ ግን ሚመጣውን ልብስ እየጠበኩ ነው ያቃተኝ ! " ሚል መልዕክት አስቀምጦለት አገኘው ። ላንተ ተራ ለሌሎች የህይወት ጉዳይ በሆኑ ነገሮች ላይ ችልተኛ አትሁን @heppymuslim29 2.7K views*¨*ɯɐɥlǝ*¨*, edited 19:33