Get Mystery Box with random crypto!

ሄላንሳን

የቴሌግራም ቻናል አርማ helansane — ሄላንሳን
የቴሌግራም ቻናል አርማ helansane — ሄላንሳን
የሰርጥ አድራሻ: @helansane
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.11K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ኦርቶዶክሳዊ ስብከቶችንና ጥበባዊ ጽሑፎችን የሚያገኙበት ምኅላፍ (ቻናል) ነው። ይቀላቀሉ! ያተርፋሉ!
#ሄላንሳን ማለት #የክብር ልብስ ማለት ነው። በቃሉ ጸንተን የክብር ልብስን ለመደረብ ያብቃን።
join us @helansane
https://telegram.me/helansane

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-01 20:51:34
እንኳን ደስ አላችሁ በዩቲዩብ የምናውቀው #ማኅቶት_ቲዩብ አሁን ደግሞ በቴሌግራም መጥቷል ለመቀላቀል ከስር ያለውን ሊንክ ንኩት።




https://t.me/+SLPMr-p0D_QzRyzI
https://t.me/+SLPMr-p0D_QzRyzI
https://t.me/+SLPMr-p0D_QzRyzI




.
8 views17:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 23:46:52 አንድም አውሬ ከባሕር ሲወጣ አየሁ፤ አሥር ቀንዶችና ሰባት ራሶች ነበሩት፥ በቀንዶቹም ላይ አሥር ዘውዶች በራሶቹም ላይ የስድብ ስም ነበረ።  ያየሁትም አውሬ ነብር ይመስል ነበር፥ እግሮቹም እንደ ድብ እግሮች፥ አፉም እንደ አንበሳ አፍ ነበሩ። ዘንዶውም ኃይሉንና ዙፋኑን ትልቅም ሥልጣን ሰጠው።  ከራሶቹም ለሞት እንደ ታረደ ሆኖ አንዱን አየሁ፥ ለሞቱ የሆነውም ቍስል ተፈወሰ። ምድርም ሁሉ አውሬውን እየተከተለ ተደነቀ፥  ለዘንዶውም ሰገዱለት፥ ለአውሬው ሥልጣንን ሰጥቶታልና፤ ለአውሬውም። አውሬውን ማን ይመስለዋል፥ እርሱንስ ሊዋጋ ማን ይችላል? እያሉ ሰገዱለት።  ታላቅንም ነገርና ስድብን የሚናገርበት አፍ ተሰጠው፥ በአርባ ሁለት ወርም እንዲሠራ ሥልጣን ተሰጠው።  እግዚአብሔርንም ለመሳደብ ስሙንና ማደሪያውንም በሰማይም የሚያድሩትን ሊሳደብ አፉን ከፈተ።  ቅዱሳንንም ይዋጋ ዘንድ ድልም ያደርጋቸው ዘንድ ተሰጠው፥ በነገድና በወገንም በቋንቋም በሕዝብም ሁሉ ላይ ሥልጣን ተሰጠው።  ከዓለምም ፍጥረት ጀምሮ በታረደው በግ ሕይወት መጽሐፍ ስሞቻቸው ያልተጻፉ በምድር የሚኖሩ ሁሉ ይሰግዱለታል። 

ጆሮ ያለው ቢኖር ይስማ። 

               የዩሐንስ ራዕይ 13÷1-9


የ 666 ትርጉሙ ምንድ ነው

ማይክሮ ቺፕስ የሚባለውስ ምንድ ነው

የአለም ፍፃሜስ መቼ ነው

ስለ አለም ፍፃሜ የሚያትተው የራዕይ መፅሐፍስ ትርጉሙ ምንድነው

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
Ŝúbŝčŕibé our youtube channel













.
5 views20:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-05 10:57:47 የእመቤታችን 120 ስሞች !
ብቸኛዋ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን
የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም 120 ስሞችን እንዲህ በማለት ትጠራታለች።
1. ሰአሊተ ምሕረት
2. ድንግል
3. እመ ብዙሃን
4. አቁራሪተ መዓት
5. የገብርኤል ብስራት
6. ንፅህተ ንጹሐን
7. ሃገረ እግዚአብሔር
8. ቅድስተ ቅዱሳን
9. ማህደረ ሰላም
10. መዓርገ ሕይወት
11. ማኅደረ ስብሐት
12. ማኅደረ ትፍስሕት
13. ቤተ ሃይማኖት
14. ብጽዕት
15. ሕሪት
16. ክብርት
17. ልእልት
18. ውድስት
19. የሰማዕታት እናት
20. የመላዕክት እህት
21. የነቢያት ትንቢት
22. የሐዋርያት ሞገስ
23. እመ ብርሃን
24. ርሕርሕተ ልብ
25. እመ አምላክ
26. የሲና እፀ ጳጦስ
27. የአዳም ተስፋ
28. የአብል ይውሕና
29. የሴት ቸርነት
30. የሔኖክ ደግነት
31. ሙጻአ ፀሐይ
32. ታቦት ዘዶር
33. እግዝትነ ማርያም
34. የቅዱስ ኤፍሬም ባራኪ
35. ምልዕተ ውዳሴ
36. ቡርክት
37. የደስታ መገኛ
38. ምእራግ
39. አዳም ቆማ
40. ጽርሕ ንጽሕት
41. ማሕደረ መለኮት
42. እሕቱ ለሙሴ
43. ገራሕቱ ለአብርሃም
44. ወለቱ ለዳዊት
45. እሙ ለአማኑኤል
46. ነያ ሰናይት
47. እምነ ጽዮን
48. መዝገበ ብርሃን
49. ጽጌ ሃይማኖት
50. ደብተራ ፍጽምት
51. ማርያም ቅድስት
52. አክሊለ ንጹሐን
53. ብርሃነ ቅዱሳን
54. ወለተ ሐና ወኢያቄም
55. መድኃኒተ ይእቲ
56. ሐመልማለ ገነት
57. ሙዳዬ መና
58. ርግበ ጸአዳ
59. ሐመልማላዊት
60. መንፈሳዊት ሃገር
61. የኖህ መርከብ
62. የሴም ምርቃቱ
63. የሴም እድል ፈንታዉ
64. የአብርሃም ዘመድ
65. ሶልያና
66. እሙ ለፀሐይ ጽድቅ
67. ምስራቀ ምስራቃት
68. በትረ አሮን
69. የገነት ኮል
70. የይስሐቅ ሽቱ
71. የያዕቆብ መሰላል
72. የዮሴፍ አረጋጊ
73. ቤዛዊተ ዓለም
74. የእሴይ ሥር
75. ወለተ ዳዊት
76. የሙሴ ጽላት
77. የአሮን ካህን ጸናጽል
78. የኢያሱ የምስክር ሐውልት
79. የጌዴዎን ጸምር
80. የሳሙኤል ሽቱ
81. የአሚናዳብ ሰረገላ
82. የዳዊት መሰንቆ
83. የሰሎሞን ቀለበት
84. የኤልያስ መሶበወርቅ
85. የኤልሳዕ ልሕኩት
86. የኢሳይያስ ትንቢት
87. የሕዝቅኤል አዳራሽ
88. ዕፀ ሕይወት
89. የሚኪያስ ኤፍራታ
90. የናሆም ፈዋሽ
91. የዘካርያስ ደስታ
92. ወለተ ጽዮን
93. ንጽሕት ጸምር
94. ደብተራ ዘትዕይንት
95. ሀገረ ክርስቶስ
96. ኪዳነ ምሕረት
97. በአታ
98. መሰረተ ሕይወት
99. ናዛዚተ ሕዙናን
100. እሕትነ ነያ
101. አንቀጸ አድሕኖ
102. መዓዛ እረፍት
103. ርግብየ ሠናይት
104. ሐረገወይን
105. አንቀጸ ብርሃን
106. ተቅዋም ዘወርቅ
107. መቅደስ
108. ሐመልማለ ወርቅ
109. ብርሃነ ሕይወት
110. ሆሕተ ምስራቅ
111. መዝገቡ ለቃል
112. ፍኖተ ሕይወት
113. ምስጢረ ስብሐት
114. መዝገበ ብርሃን
115. ምልእተ ክብር
116. ምልእተ ፍስሐ
117. ምልእተ ፀጋ
118. ጽላተ ኪዳን
119. ጽላተ ሕግ
120. ዳግሚት ሰማይ
3.3K views07:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-24 20:00:00 አለምን እየመራት ያለው ሰይጣን ማን ነው?

“ወደድንም ጠላንም ህይወታችን ለፈጣሪ ባለን የምስጋና መጠን ይወሰናል። ህይወታችንን እጅግ መልካም ለማድረግ አልያም እርግማን ወደሞልው የሰቀቀን ኑሮ ለመለወጥ የሚያስችለን የገዛ አመለካከታችን ነው። አንዳንዶቻችን በቤታችን ጓሮ የተተከለውን ጽጌሬዳ ስንመለከት ጽጌሬዳው በእሾህ መወረሱ ያበሳጨናል፤አንዳንዶች ደግሞ እሾሁ ጽጌሬዳ ማብቀሉ ይገርማቸዋል። ሁሉ ነገር እኛ በሚኖረን የህይወት መነጽር ይወሰናል።...ሙሉውን ለማንበብ
856 views17:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-18 13:40:19 #5ቱ ሀዘናት
የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም 5ቱ ሀዘናት አንድ አምላክ በሚሆን በአብ፣ በወወልድ፣ በወመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን። የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ፭ቱ ታላላቅ ኀዘናት ማን ማን ናቸው ቢሉ? ።
፩ኛ - ስምዖን በቤተ መቅደስ ትንቢት በተናገረ ጊዜ።
፪ኛ - ከቤተ መቅደስ ፈልጌህ ባጣሁህ ጊዜ።
፫ኛ - በጲላጦስ አደባባይ በገረፉህ ጊዜ።
፬ኛ - በዕለተ ዓርብ በሰቀሉህ ጊዜ።
፭ኛ- ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ገንዘው ወደ አዲስ መቃብር ባወረዱህ ጊዜ።
..
ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን
በእኔ ምክንያት ካገኙሽ ኅዘናት የትኛው ይበልጣል ብሎ በጠየቃት ጊዜ ???
እመቤታችንም ልጄ ወዳጄ ሆይ ባንተ ምክንያት ካገኙኝ ኅዘናት እነዚህን አምስቱ ይበልጣሉ ብላ እመቤታችን የጠቀሰቻቸው ታላላቅ ኅዘናት እነዚህ ሲሆኑ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እነዚህን ያንችን ኅዘናት እያሰበ የጸለየ ኃጢአቱን ይቅር እለዋለሁ ብሎ ቃል ኪዳን ሰጥቷታል።

፩ኛ - ስምዖን በቤተ መቅደስ ትንቢት በተናገረጊዜ።
..
ስምዖን የተባለው፦ አረጋዊው ስምኦን ነው የእመቤታችን ሐዘን የሚጀምረው ገና አንድዬ ልጇን ከመውለዷ በስምተኛው ቀን ነው ቤተመቅደስ ይዛው በሄደች ጊዜ አረጋዊው ስምዖን “በአንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል (ልጅሽ በቀራንዮ ይሞታል)” ሉቃስ 2፥34-35 ብሎ በነገራት ጊዜ ድንግል ማርያም አምርራ አዘነች አለቀሰች።
እነሆ፥ የብዙዎች ልብ አሳብ ይገለጥ ዘንድ፥ ይህ በእስራኤል ላሉት ለብዙዎቹ ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው ለሚቃወሙትም ምልክት ተሾሞአል፥ በአንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል አላት። ሉቃ (2፡34-35)

፪ኛ - ከቤተ መቅደስ ፈልጌህ ባጣሁህ ጊዜ።
..
ወላጆቹም በያመቱ በፋሲካ በዓል ወደ ኢየሩሳሌም ይወጡ ነበር። የአሥራ ሁለት ዓመ ልጅ በሆነ ጊዜ፥ እንደ በዓሉ ሥርዓት ወደ ኢየሩሳሌም ወጡ፤ቀኖቹንም ከፈጸሙ በኋላ፥ ሲመለሱ ብላቴናው ኢየሱስ በኢየሩሳሌም ቀርቶ ነበር፥ ዮሴፍም እናቱም አላወቁም ነበር። ከመንገደኞች ጋር የነበረ ስለመሰላቸው የአንድ ቀን መንገድ ሄዱ፥ ከዘመዶቻቸውም ከሚያውቋቸውም ዘንድ ፈለጉት፤ባጡትም ጊዜ እየፈለጉት ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ። ከሦስት ቀንም በኋላ በመምህራን መካከል ተቀምጦ ሲሰማቸውም ሲጠይቃቸውም በመቅደስ አገኙት፤ የሰሙትም ሁሉ በማስተዋሉና በመልሱ ተገረሙ። ባዩትም ጊዜ ተገረሙ፥ እናቱም። ልጄ ሆይ፥ ለምን እንዲህ አደረግህብን? እነሆ፥ አባትህና እኔ እየተጨነቅን ስንፈልግህ ነበርን አለችው። ሉቃ (2፡41-48)
፫ኛ - በጲላጦስ አደባባይ በገረፉህ ጊዜ።

በዚያን ጊዜም ጲላጦስ ኢየሱስን ይዞ ገረፈው። ወታደሮችም ከእሾህ አክሊል ጐንጕነው በራሱ ላይ አኖሩ ቀይ ልብስም አለበሱት፤ እየቀረቡም። የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን ይሉት ነበር፤ በጥፊም ይመቱት ነበር። ጲላጦስም ደግሞ
ወደ ውጭ ወጥቶ። እነሆ፥ አንዲት በደል ስንኳ እንዳላገኘሁበት ታውቁ ዘንድ እርሱን ወደ ውጭ አወጣላችኋለሁ አላቸው። ኢየሱስም የእሾህ አክሊል ደፍቶ ቀይ ልብስም ለብሶ ወደ ውጭ ወጣ። ዮሐ (19፡1-5)

፬ኛ - በዕለተ ዓርብ በሰቀሉህ ጊዜ።
..
ኢየሱስንም ይዘው ወሰዱት፤ መስቀሉንም ተሸክሞ በዕብራይስጥ ጎልጎታ ወደ ተባለው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሉት ወጣ። በዚያም ሰቀሉት፥ ከእርሱም ጋር ሌሎች ሁለት፥ አንዱን በዚህ አንዱን በዚያ ኢየሱስንም በመካከላቸው ሰቀሉ። ጲላጦስም ደግሞ ጽሕፈት ጽፎ በመስቀሉ ላይ አኖረው፤ ጽሕፈቱም። የአይሁድ ንጉሥ የናዝሬቱ ኢየሱስ የሚል ነበረ።ኢየሱስም የተሰቀለበት ስፍራ ለከተማ ቅርብ ነበረና ከአይሁድ ብዙዎች ይህን ጽሕፈት አነበቡት፤ በዕብራይስጥና በሮማይስጥ
በግሪክም ተጽፎ ነበር።ስለዚህ የአይሁድ ካህናት አለቆች ጲላጦስን። እርሱ። የአይሁድ ንጉስ ነኝ እንዳለ እንጂ የአይሁድ ንጉሥ ብለህ አትጻፍ አሉት። ጲላጦስም። የጻፍሁትን ጽፌአለሁ ብሎ መለሰ። ዮሐ. (19፡17-22)
join us @helansane
፭ኛ- ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ገንዘው ወደ አዲስ መቃብር ባወረዱህ ጊዜ።
..
ከዚህም በኋላ አይሁድን ስለ ፈራ በስውር የኢየሱስ ደቀ መዝሙር የነበረ የአርማትያስ ዮሴፍ የኢየሱስን ሥጋ ሊወስድ ጲላጦስን ለመነ፤ ጲላጦስም ፈቀደለት። ስለዚህም መጥቶ የኢየሱስን ሥጋ ወሰደ።ደግሞም አስቀድሞ በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ መቶ ንጥር የሚያህል የከርቤና የእሬት ቅልቅል ይዞ መጣ።የኢየሱስንም ሥጋ ወስደው እንደ አይሁድ አገናነዝ ልማድ ከሽቱ ጋር በተልባ እግር ልብስ ከፈኑት።በተሰቀለበትም ስፍራ አትክልት ነበረ፥ በአትክልቱም ማንም ገና ያልተቀበረበት አዲስ መቃብር ነበረ።ስለዚህ መቃብሩ ቅርብ ነበረና ስለ አይሁድ ማዘጋጀት ቀን ኢየሱስን በዚያ አኖሩት። ዮሐ (19፡38-42)

እነዚህን አምስቱን የእመቤታችን ሐዘናት እያሰበ ያዘነ ዝክሯን የዘከረ በአማላጅነቷ የታመነ ዋጋው ከቶ አይጠፋበትም፡፡

ቅድስት ሆይ ለምኝልን
ቅድስት ሆይ ለምኝልን
ቅድስት ሆይ ለምኝልን
።።።አሜን አሜን።።።
ይህ ኦርቶዶክሳዊ ስብከቶችንና ጥበባዊ ጽሑፎችን የሚያገኙበት ምኅላፍ (ቻናል) ነው። ይቀላቀሉ! ያተርፋሉ! #ሄላንሳን ማለት #የክብር ልብስ ማለት ነው። በቃሉ ጸንተን የክብር ልብስን ለመደረብ ያብቃን።
join us @helansane
https://telegram.me/helansane
1.3K views10:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-22 20:00:00 በኢትዮጵያ የተሰወሩ ፒራሚዶች ያሉበት ቦታ ታወቀ !



እነዚህ ፒራሚዶች እና ቤተ መቅደሶች የሚገለጡበት ዘመን ታወቀ


እውነት በኢትዮጵያ መሬት በሰማያዊ ሀይል ተቀብረው የሚገኙ ፒራሚዶች እና ቤተ መቅደሶች አሉ ? እንዴትስ ተሰሩ ?

ስለ እነዚህ ፒራሚዶችና ቤተመቅደሶች አስገራሚ ምስጢሮች


በቅዱሳን አባቶቻችን ስለተሰወረው ድንቅ መፅሐፍ


እነዚህን እና ሌሎች ሚስጢራትን ስለ ኢትዮጵያ ስውር ቤተ መቅደሶች እንዲሁም ፒራሚዶች ማወቅ ከፈለጉ በ Youtube ቻናላችን ሙሉ ትምህርቱን ማግኘት ትችላላቹ ከስር ያለውን Open የሚለውን ተጭነው ! እንዲሁም ሌሎች ድንቅ ፕሮግራሞችንም ማግኘት ይችላሉ በዛውም የ Youtube ቻናላችንንም Subscribe ያርጉ !




ይህን ይጫኑት ... ይህን ይጫኑት
.
█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█
764 views17:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-20 18:56:51 #የፈተነችህ የዝሙት ጾር ብትርቅህ ተጠንቀቅ!!!
(#ካብኩህ ካብኩህና ቁልቁል አፈረጥኩ!!!)

። እንኳን አደረሳችሁ ።
ውድ የሄላንሳን ቻናል ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ? ቸር አምላክ እንደ እኛ ኃጢአትና በደል ብዛት በፊቱም እንደ መርከሳችን ሳያጠፋን እድሜ ለንስሃ እየሰጠን ይኸው አለን። መሃሪ የሰላም አባት ልዑለ ባህርይ ለሆነው #ለእግዚአብሔር ክብር ምሥጋና ይግባውና ሄላንሳን ማዕዳችሁ ዛሬ በአብይ ጾም አራተኛ ሳምት ጅማሬ ማዕድዋን ልታቀርብልኝ የቀድሞን ውብ የትውስታ ማዕድ ይዛ በድጋሜ አቅርባለች የጎደለ ማዕድ እንኳን ቢኖር ከቅድም ውስንነት ነው ብላችሁ ያቀረበችውን ተመገቡላት ።፤ ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን። አሜን
@helansane
የክፋት ስልት ባለቤት የሆነው የጨለማው ዓለም ግዞት ስልጣን የተሰጠው የክፋት አባት የዝሙት ጠንሳሽ የሆነው ዲያብሎስ በዘመናችን ስልቱ የበዛ መንገዶች እየተጠቀመ የእኛን ዘመን እንዲህ አድርጎታል! #እንደምናየው የክፍት ስልት ባለቤቱን በግድ የለሽነት በጣለብንም ዐዚም መንቃት አቅቶን እየወደቅን ያለን ዛሬ....አሁን የመንፈስ ዓይናችንን እንግለጥ ከተኛንበት እንቃና የመዳን ቀን ዛሬ ነው ወደ ካህናት አባቶቻችን እንሩጥ በንስሃ እንባ እንታጠብ የሰላም ንጉሡ ሳይመጣ!!!

ብዙ ጊዜ በወጣትነት እድሜ ላይ ያለን ሰዎች ፈተና ይህ ነው። ዝሙትና መከራው ስለዚህ በዛሬዋ ንቃተ ህሊናን ሚሰጥ ማዕድ እንመገባለን ከአበው ምክርና ተግጻጽ።
ዲያብሎስ ሁሌም አንድን(አንዲትን) ወጣት በዝሙት ክፍኛ በመዋጋት ያደክመውና አልፎ አልፎ ይጥለዋል። በዚህ ጊዜ ወደ ንስሃ አባቶች አምርቶ ንስሃ በመግባት ይህን ኃጢአት
ሊያስፈጽሙት ከሚችሉት ምክንያቶች ሁሉ #በማንበብ ፥ ቃለ እግዚአብሔርን አብዝቶ በመስማት እራሱን በትጋት መጠበቅ ይጀምራል። በተመሳሳይ ጊዜ ከእንባ ጋራ በጸሎት ወደ እግዚአብሔር በመጮህ ያድነው ዘንድ ይማጸናል። በዚህ ጊዜ የዝሙት አባት የሆነው ዲያብሎስ እንደምን ሊፈትነው ይችላል? ይህን መመለስ ታላቅ ግብዓት አድርጎ ስልቱን ሚቀይረውን ዲያብሎስን ግን አያስተውልም። የቀደመውን የዝሙት ፈተና ፍጹም ለጊዜው ይተወውና በሌኛው የከፋ ኃጢአትም ሊጥለው ያዘጋጀዋል ለእርሱ የአንደኛው ፍጻሜ ለሁለተኛው ኃጢአት ጅማሬ ይሆንለታል!! #ለማይነቃ ክርስቲያን።
@helansane
ከዚህ በኃላ ሚሰራው ስራ ለአመታት ያክል ወጣቱን በዝሙት እንዳይወድቅና እንዲወድቅም ምክንያት ሚሆኑትን ነገሮች ከሥሩ በማጥፋት ስለ ዝሙት #ማሰብ እንኳ እስኪያቆም ድረስ እርግፍ አድርጎ ይተወዋል በሌላኛው #በኩራት ኃጢአት ሊጥለው ስራውን ይጀምራል። አብልጦ ቅዱሳን መጽሐፍትን እንዲያነብ መልካም ስራዎችን በህይወቱ እንዲያበዛ ይራዳዋል የበለጠ ጨምሮ ጨምሮ ጸሎቱን ሁሉ እንዲያደርግ ያበረታዋል።(ካብኩህ ካብኩህና ቁልቁል አፈረጥኩህ) እያለ ላንተ ሚዘፍንልህን ግጥም ያዘጋጃል እርሱ ደራሲው የክፋት አባት ዲያብሎስ
@helansane
ወጣቱ በአዲሱ የስልት መንገድ መፈተኑን ሲጀምር ሰዎችን ተናጋሪ በመሆን ይጀምራል። እንዴት በነብያት ጾም ጊዜ አትጾምም እናትና አባትህ ቤተሰቦችህ አይጾሙም፥ አንተስ ለምንድነው ማጾመው? አንተ ለምንድነው ንስሃ ማትገባው? አንተ ለምንድነው ቁርባን ማትቀበለው? እያለ ሌሎችን ክፉኛ እንዲኮንንና እንዲገጽጽ ዲያብሎስ ያማክረዋል። ዘለፋው አይሎ ሌሎችን ከእግዚአብሔር በመራቃቸው ሊሰድባቸውና ሊጠላቸው ይጀምራል። ልቡ በፍጹም #ኩራት ይደፈናል #በጽድቅ ስም ሊሳደብ፥ በቁጣ ሊናገር፥ ፍጹም አላዋቂነቱን ሊያሳይ ይነሣል። በሉቃ ወንጌል(18፥11) እንዳለው ፈሪሳዊ "#እግዚአብሔር ሆይ እንደ ሌላ ሰው ሁሉ #ቀማኞችና #ዓመፀኞች #አመንዝሮችም ወይም እንደዚህ ቀራጭ ስላልሆንኩ አመሰግንሃለሁ"" በማለት ይህም ወጣት በእግዚአብሔር ፊት ሊጸልይ ይጀምራል። ስለዚህ ቀደም ብሎህ የዘፈን ግጥሙን የወጣቱን አካሄድና ፍጥነት አይቶ በቶሎ ዜማውን የቀመረው ዲያብሎስ እንዲህ ይላል ብትጠይቀው ፈገግ እያለ ከዝሙት ስለ ተገላገለው ወጣት ""በዝሙት ኃጢአት ውስጥም ሆነ በኩራት ኃጢአት ውስጥ ሞት አለ። የሁለቱም ደመውዝ ሞት ነው።""እያለ ቅላጼውን ይጨምራል በክርፋታም ድምጹ #ካብኩህ ካብኩህና ቁልቁል አፈረጥኩ!!!!!!!!!!! እያለ ይቀጥላል
@helansane

#ውድ የሄላንሳን ቤተሰቦቼ የኃጢአት ፈተናዎቻችን ከእኛ ቢርቁ #እንጠንቀቅ!!! በከፋው ኃጢአት ሊጥለን ፍጹም የማይተወን ጠላት አለንና #እንንቃ #በኩራት ታጅረን ሌሎችን ከምንናገር ይልቅ በኃጢአት ውስጥ ሆነን በደለኝነታችንን እያመንን ከአምላክ ፊት ለምህረት መቆም ይሻላልና እድፋችን(ኃጢአታችን) በዝቶ የሌሎችን አንዲት እድፍ ለመፋቅ አንሩጥ።
#ሼር በማድረግ እንማማር
#የሰላም አባት የሰላም አለቃ ልዑል #እግዚአብሔር ለሀገራችን ሰላምና ምህረትን ይላክልን ቅድስት ቤተክርስቲያንን ይጠብቅልን ለሁላችንም የንስሃ እድሜ ያድለን። አሜን
504 views15:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-17 12:20:57 አባ ኪሮስ አባ ኪሮስ አባቱ ንጉስ ዮናስ እናቱ አንስራ ይባላሉ፡፡ ሀገሩ ሮም ነው፡፡ ወላጆቹ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ደጋግ ቅዱሳን ነበሩና አቡነ ኪሮስ በታህሳስ 8 ወለዱ፡፡ አቡነ ኪሮስ የመጀመሪያ ስሙ ዲላሶር ይባል ነበር፡፡ በኋላ አባቱ ከሞተ በኋላ ሀብቱን ከወንድሙ ተካፍሎ ለድሆች መጽውቶ ዓለምን ንቆ መንኖ ሄደ፡፡ ከአባ በቡነዳ ገዳም ገባ፡፡ በ17 ዓመቱ ሥርዓተ ምነኩስናን ተማረ፡፡ በአባ በቡነዳ እጅ መነኮሰ፡፡ ከዚህ በኋላ በጾም በጸሎት ተወስኖ ኖረ፡፡ስለ ዓለም መከራ ለ40 ዘመን ተኝተው ሲጸልዩ እላያቸው ላይ ሳር በቅሎባቸው ሳለ መላእክት መጥተው ተነስ ቢሉት አዳም የፍጡር ቃል ሰምቶ ወድቀዋል ጌታዬ ድምጹን ያሰማኝ አላቸው በኋላ ኪሩቤል አንስቶ ወስዶ ገነት አሳይተውት ጌታችንም ቃል ኪዳን ሰቷቸዋል። @helansane

ቃል ኪዳናቸውም ፡- መካኖች ልጀ የሌላቸው ገድሉን አቅፈው ቢያለቅሱ ጸበሉን ቢጠጡ ስምህን ቢጠሩ፤ የመካኒቱን ማህጸን እከፍታለሁ፡፡ የሚሞትባቸውን እንዳይሞተባቸው አደርጋለሁ፡ በንጹ ገንዘቡ ቂምና በቀል ሳይዝ በህግ በስጋውና በደሙ የጸና ሰው በስምህም በተሠራው ቤተክርስቲያን ጧፍ ዘይት ያበራ መገበሪያ ያመጣውን ልጅ አሰጠዋለሁ፡፡ ብሎ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ ከዚም በኋላ በተወለዱ 270 ዓመታቸው በዛሬዋ ዕለት ሐምሌ 8 አርፈዋል። ይህ ኦርቶዶክሳዊ ስብከቶችንና ጥበባዊ ጽሑፎችን የሚያገኙበት ምኅላፍ (ቻናል) ነው። ይቀላቀሉ! ያተርፋሉ!
#ሄላንሳን ማለት #የክብር ልብስ ማለት ነው። በቃሉ ጸንተን የክብር ልብስን ለመደረብ ያብቃን።
join us @helansane
https://telegram.me/helansane
500 views09:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-16 09:19:04 #የአባ እንጦንስ ምክሮች
join us @helansane
✞ #ከዕለታት በአንድ ቀን አባ ፓምቦ አባ እንጦስን "ማድረግ ያለብኝ ነገር ምንድን ነው?" ብሎ ይጠይቃል። አባ እንጦስም እንዲህ ሲል መለሰለት "በራስህ ጽድቅ አትታመን፤ ላለፈው ነገር አትጨነቅ፤ ይልቁኑ አንደበትህንና ሆድህን ግዛ።"
✞ #አባ እንጦስ በአንድ ወቅት እንዲህ አለ፦ "በዚች ምድር ላይ ስንኖር ሕይወታችንም ሆነ ሞታችን ከባልጀራችን ጋር ነው። ወንድማችንን ገንዘብ ካደረግነው እግዚአብሔርን ገንዘብ እናደርጋለን፤ ወንድማችንን ከተውነው ግን በራሳችን ላይ ኃጢአትን እናመጣለን።"
join us @helansane
✞ # በአንድ ወቅት አንድ ወንድም አባ እንጦስን "ጸልይልኝ" በማለት ይጠይቃል። እንጦስም "አንተ ራስህ ጥረት የማታደርግና ወደ እግዚአብሔር የማትጸልይ ከሆነ እግዚአብሔር ምሕረት ሊያደርግልህ አይችልም" አለው።
✞ #ከንቱ ውዳሴን ከእርሱ ለማራቅ አባ እንጦንስ እንዲህ ብሎ ይጸልይ ነበር፦ "እግዚአብሔር ሆይ አፈርና ትቢያ ሆኜ ሳለ ጻድቅ አድርገው ከሚቆጥሩኝ ሰዎች አድነኝ።"
✞ #ኃጢአታችንን እኛ እያሰብን የምንጸጸት ከሆነ እግዚአብሔር ይረሳልናል፤ ኃጥያታችንን እኛ እረስትን የምንጸና ከሆነ እግዚአብሔር ያስብብናል።
join us @helansane
✞ #ብዙ ጊዜ ሰዎች ብልህ ነን እያሉ ይሳሳታሉ። ነገር ግን ብልህ የሚባሉት ብዙ የተማሩና ብዙ ያነበቡ ብዙ የሚናገሩ ብቻ አይደሉም። ይልቁንም ጠቢባን የሚባሉት ብልህ ነፍስ ያላቸው፤ የእግዚአብሔርንና የሰይጣንን ለይተው ለእግዚአብሔር ሆነው የሚኖሩ ናቸው። ፍጹም ምልዓተ ኃጢአትንና ከጦር ይልቅ የሚወጉ የኃጢአት እሾሆችን ከራሳቸው ላይ የነቀሉ ናቸው ጠቢባን።
✞ # ጠቢባንስ እግዚአብሔርን ያለጥርጥር በሙሉ ልብ የሚያምኑት፤ አምነውም እንደ ፈቃዱ የተከተሉት፤ በክንፈ ጸጋ ተመስጠው ከልብ በሚወጣ ውዳሴ ከእርሱ ጋር ተዋሕደው የሚኖሩ ናቸው። የነፍሳቸውን ረብሕ ጥቅም አውቀው ዕለት ዕለት ያንን የሚለማመዱ በእውነት ጠቢባን እነዚህ ናቸው።
✞ #የጋለ ብረትን ለመቀጥቀጥ የሚነሣ ሰው አስቀድሞ በብረቱ ምን ለመሥራት እንዳሰበ መወሰን አለበት፤ መጥረቢያ፥ ሰይፍ፥ ወይስ ማጭድ? እኛም በምን ዓይነት የሕይወት መስመር ፍሬ ለማፍራት እንዳሰብን አስቀድመን ልቡናችንን ማዘጋጀት አለብን፡፡
✞ #ዘወትር በዐይንህ ፊት ፈሪሃ እግዚአብሔር ይኑር፤ ሕይወትና ሞት የሚሰጠውን አዘክረው፡፡ ዓለምንና በዓለም ያለውን ሁሉ ጥላው፤ ከሥጋ የሚመጣውን ደስታና ሰላም አትሻ፤ ለዚህኛው ኑሮ ሙትና ለእግዚአብሔር ሕያው ሁን፤ ለእግዚአብሔር ቃል የገባኸውን አትርሳ፤ ያም በፍርድ ቀን ካንተ ይፈለግብሃል፡፡ ረኀብን በጸጋ ተቀበለው፤ ተጠማ፥ ተራቆት፥ ንቁና በኀዘን የምትኖር ሁን፡፡ በልቡናህ አልቅስና ጩኽ፤ ለእግዚአብሔር የምትመች መሆን አለመሆንህን ፈትን፤ ሥጋህን ቀጥተህ ነፍስህን ታድናት ዘንድ፡፡
✞ #የቱንም ያህል መከራ ቢወድቅብህ የቱንም ያህል በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ብታልፍ ይህንን ለጌታዬ ለመድኃኒቴ ለኢየሱስ ክርስቶስ ስል እቀበላለሁ በል። ቀላል ይሆንልሃል። የጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ኃይል ነውና፣ በእርሱ ማዕበሉ ጸጥ ይላል ሰይጣንም ይሸሻል።
✞ #ለሃይማኖት መከራከር፤ ጠበቃ መሆን፤ መዋጋት ብሎም መሞት አይከፋም ሁልጊዜ ለሃይማኖት መኖር ግን ከሁሉ የበለጠ መስዋዕትና ክብር ያለው ሕይወት ነው፡፡
ይህ ኦርቶዶክሳዊ ስብከቶችንና ጥበባዊ ጽሑፎችን የሚያገኙበት ምኅላፍ (ቻናል) ነው። ይቀላቀሉ! ያተርፋሉ!
#ሄላንሳን ማለት #የክብር ልብስ ማለት ነው። በቃሉ ጸንተን የክብር ልብስን ለመደረብ ያብቃን።
join us @helansane
https://telegram.me/helansane
አምላከ ቅዱሳን ልዑል እግዚአብሔር ሳምንቱን የሰላም የፍቅር የይቅርታ እንዲሁም ከምናያቸውና ከምንሰማቸው መጥፎ ነገሮች በሙሉ በምህረቱ ብዛት ይጠብቀን። ሁላችንም ስለ #ቅድስት ሀገራችን ኢትዮጵያ ሰላም እንጸልይ። ቸር ያቆየን
1.5K viewsedited  06:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-12 22:30:22 በኢትዮጵያ የተሰወሩ ፒራሚዶች ያሉበት ቦታ ታወቀ !



እነዚህ ፒራሚዶች እና ቤተ መቅደሶች የሚገለጡበት ዘመን ታወቀ


እውነት በኢትዮጵያ መሬት በሰማያዊ ሀይል ተቀብረው የሚገኙ ፒራሚዶች እና ቤተ መቅደሶች አሉ ? እንዴትስ ተሰሩ ?

ስለ እነዚህ ፒራሚዶችና ቤተመቅደሶች አስገራሚ ምስጢሮች


በቅዱሳን አባቶቻችን ስለተሰወረው ድንቅ መፅሐፍ


እነዚህን እና ሌሎች ሚስጢራትን ስለ ኢትዮጵያ ስውር ቤተ መቅደሶች እንዲሁም ፒራሚዶች ማወቅ ከፈለጉ በ Youtube ቻናላችን ሙሉ ትምህርቱን ማግኘት ትችላላቹ ከስር ያለውን Open የሚለውን ተጭነው ! እንዲሁም ሌሎች ድንቅ ፕሮግራሞችንም ማግኘት ይችላሉ በዛውም የ Youtube ቻናላችንንም Subscribe ያርጉ !




ይህን ይጫኑት ... ይህን ይጫኑት
.
█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█
401 views19:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ