2023-01-14 17:46:39
ላባና መልኩ!!!
◆ላባ የያዕቆብ በጣም የቅርብ የስጋ ዘመዱ ነበር፦ በሰውኛ "አጎቱ"
◆ነገር ግን ለያዕቆብ የነበረው ዓላማ በባርነት እና በማታለል ዘመኑንና ጉልበቱን መብላት ።
◆በምንም ተዓምር ያዕቆብ እንዲለወጥ፥እንዲያድግ፥ ለራሱ የሆነ ነገር እንዲኖረው አይፈልግም ነበር።
◆ያዕቆብ ግን በእግዚአብሔር ፍርሀት ደከመኝ፣ሰለቸኝ ሳይል 20 ዓመት አገለገለው።
◆ይህን ሁሉ ግን የአብርሀም አምላክ ይመለከት ነበር ►►ግፈኞች የማይገባቸው እውነት ይህ ነው!!!!
◆ ላባ ያልከፈለውን ደመወዝ ፈጣሪው ተዓምረኛ በሆነ መንገድ ለያዕቆብ ከፈለው►► ጌታ ፃድቅ ፈራጅ ነው ዛሬም ይከፍላል!!!
◆ይህን ጊዜ ክፉው ላባ ተቆጣ ፊቱ ተቀያየረ።
►ስትጎሳቆል፣ስትደኸይ ፣ ባዶ ስትሆን ምንም የማይመስለው፡ ቀና ስትል ማጉረምረም ይጀምራል ►►ይገርማል!!!!!!
◆ታዲያ ጊዜው ደረሰና አምላኩ "በቃህ ከዚህ ሰው ቤት ውጣ እና እኔ ወደምልህ ሂድ" በማለት ለያዕቆብ ምሪት ሰጠው።
◆ያዕቆብም አምላኩ የሰጠውን ይዞ ጉዞ ጀመረ።
◆ያዕቆብ ሲወጣ በአምላኩ ትዕዛዝ ስለነበረ ክፉ ለሚያስብበት ላባ የመናገር ግዴታ የለበትም!! ►►ዛሬም ሰማይ ውጡ ካላችሁ ለክፉዎች የማሳወቅ ግዴታ የለባችሁም!➯ከያዕቆብ ይህን ተምረናል።
◆ይህን ሲሰማ ላባ ሰይፍ ታጥቆ ያዕቆብን ለማሳደድ የሰባት ቀን መንገድ ተጓዘ።
◆በጣም የሚገርመው ክፉ ሰዎች አምላክህ እንኳን ሲያሳካልህ እና መንገድህን ሲያቀናልህ አንተን ለማዋረድ የሚከፍሉት ዋጋ እጅግ ታላቅ መሆኑ ነው!!!
◆ላባ አንድም ቀን ለያዕቆብ ስኬት አንድ እርምጃ መንገድ ሳይሄድ ያዕቆብን ለመጣል የሰባት ቀን መንገድ ተጓዘ።
◆ጌታም ላባን በደንብ እስኪደክመው አስጓዘው።►►ዛሬም ክፉዎች ያልገባቸው ነገር ሰይፍ ታጥቀው እና ሀይል አሰባስበው እየሮጡ ያሉት ለድካም ብቻ መሆኑን ነው።➯➯ ውጊያው ከያዕቆብ ጋር ሳይሆን ውጣ ካለው ከአምላኩ ጋር ነው! ክፉዎች► ''take care''!!!
◆ላባ ብዙ ደክሞ ያዕቆብጋ ሲደርስ➯ እግዚአብሔር አነጋገረው!!! ጠላት አገኘሁት ተሳካልኝ ብሎ ብዙ ከለፋና አጠገቡ ከደረሰ በኋላ ለካስ የጦር መሳሪያና ሰራዊት የሌለው ያዕቆብ የሚዋጋለት፥የሚሟገትለት እና የማይተኛ ብርቱ ጠባቂ አለው!!!!!
◆እናም እግዚአብሔር ለላባ ቀጭን ትዕዛዝ ሰጠው! እንዲህ ሲል፦"ያዕቆብን እንኳን በሰይፍ መንካት በክፉ ነገር እንዳትናገረው ተጠንቀቅ!!!!" አለው።►►ዛሬም ጠላታችሁን አስለፍቶ ጌታ ያስጠነቅቅላችኋል!!!
◆ አይ ብሎ ደግሞ እንደፈርኦን ገስግሶ ካልያዝኳችሁ፣ካላንበረክዃችሁ ካለ ያው በንጋታው በባህሩ ዳርቻ እናንተ እየዘመራችሁ የሱን በድን ታያላችሁ ማለት ነው። "እግዚአብሔር ተዋጊ ነው ስሙም እግዚአብሔር ነው!!" ጠላታችሁን ከነፈረሶቹ ወደ ባህር ይጥላቸዋል። እናንተ ግን ከሚመራችሁ ጌታ ጋር ጉዟችሁን በድል፣በስኬት፣ በዝማሬ፣በአምልኮ መቀጠል ነው።
◆ላባ ሁለተኛ ዘዴ ዘየደ ➯ ከያዕቆብ ጋር እግዚአብሔር እንዳለና የማይሸነፍ፣የሚበዛ፣ ኃያል የሚሆን መሆኑን ሲያውቅ ፦ "ስለምን በስውር ሸሸህ? ከእኔም ከድተህ ስለምን ኮበለልህ? በደስታና በዘፈን በከበሮና በበገና እንድሰድድህ ለምን አልነገርኸኝም?
²⁸ ወንዶቹንና ሴቶቹን ልጆቼን እንድስም ስለ ምን አልፈቀድህልኝም? ይህንም በስንፍና አደረግህ። አለው።
◆እንኳን ስሞ ሊሸኘው ቢቻለው ራቁቱን ነበር የሚያስቀረው ግን የያዕቆብን ድል ሲመለከት
"ክፉ አደርግባችሁ ዘንድ ኃይል ነበረኝ፤ ነገር ግን የአባታችሁ አምላክ ትናንት፦ ያዕቆብን በክፉ ነገር እንዳትናገረው ተጠንቀቅ ብሎ ነገረኝ" አለ። ►►ዛሬም የክፋት ሀይሉን አሟጦ ሲጨርስ ጠላትህ መጥቶ በፍቅር ቃል ሊያወራህ ይሞክራል!!! "God is great!!!!" ➯➯➯➯ቀጣይ ዘዴ ዘየደ እናም፦
◆የላባ የመጨረሻው አማራጭ ያዕቆብን ስለፈራ የሀውልት ምልክት አድርጎ "ከዚህ አልፈህ እንዳትጎዳኝ ፡ ቃል ኪዳን ግባልኝ አለው" ►►እግዚአብሔር ሲያሸንፍልህ የጠላት አማራጭ አንተን መማፀን ብቻ ነው!!!
❖ሲደመደም ፦ ለእግዚአብሔር ድምፅ እንታዘዝ፣ ጦርነታችንን ለእርሱ እንስጥ፣ ለነ ላባ ቦታ አለመስጠት፣ ከጌታ ጋር ጉዞን መቀጠል እና ላባ በፍርሀት ስለተዋጠ በስጋ እንደማንጎዳው ዋስትና መስጠት (ይጋርሰሀዱታ)!!!
◆የላባ ሀይል ጣዖት፣ገንዘብ፣ሰይፍ ፣ ተንኮል እና ፍጥረታዊ ነገር ብቻ ነው የያዕቆብ ሀይል ግን የፍጥረታት ፈጣሪ እና ኤልሻዳዩ ነው።
►► That was their difference!!!!!
◆ከሌሎች ልዩነት መፍጠሪያ አቅማችንን እግዚአብሔርን እናድርግ ድሉ የኛ ይሆናል።
➯➯እግዚአብሔር ቅን ፈራጅ እና ፃድቅ ነው!!!
➯➯የላባን መልክ እና አካሄዱን እንወቅ!!!!
!!ዘፍ ፥31 ►► ይነበብ!!
መልካም ቀን!!!!
5 viewsCyrus By Jesus, 14:46