2022-07-09 07:39:22
የወፎቹ ዝማሬ ከእንቅልፌ አነቃኝ
ለመነሳት ልቦናየ ቢፈቅድም
አካሌ ግን ከአልጋየ ጋር መተሻሸቱን ወደደው ።
የብርድ ልብሴን ሙቀት አስቤ የውጩን ቅዝቃዜ በሀሳቤ ስቃኝ የአልጋየ ሙቀት በለጠብኝ።
በምርጫ ጋጋታ ብታጠርም የመረጥኩት ግን ምቾቴን ነበር ።
ከሰፈራችን በቅርብ እርቀት ከሚገኘው አድባር የቅዳሴ ድምፅ ይሰማኛል።
በዛች ቅፅበት የአከራየ በር ሲከፈት
ተሰማኝ ።
አከራየን አለማድነቅ አልችልም፤
ስንፍና የሚባል ነገር አልፈጠረባቸውም
ማንም ሳይቀሰቅሳቸው ይነሳሉ
ማንም ሰዐት ሳይነግራቸው በተፈጥሮ ተመርተው ሰዐቱን አያዛንፉም።
በሳቸው ስደነቅ አካሌን ከአልጋየ መነጠል አለመቻሌ የራሴን ስንፍና አሳበቀብኝ ።
በሀሳብ ብዙ ተጉዠ በአካል ግን አሁንም ከኋላ ነኝ ።
እንዲው ከአልጋየ ጋር እየተሻሸው ሰዐታት ነጎዱ
መተኛትን ምርጫየ ባደርግም
የተረፈኝ መገላበጥ እንጂ እንቅልፍ በአይኔ አልዞረም
በመገላበጥ ውስጥ ሁኘ መገላበጡ በራሱ ሰለቸኝ ።
እንደምንም ከአልጋየ ተስፈንጥሬ ተነሳው
የሌሊት ልብሴን አወላልቄ ፎጣ አሸርጨ ልተጣጠብ ወጣው ።
ውሀውን ለመንካት ስግደረደር ለትንሽ ደቂቃ ቆየው
እጄን ከዛም ፊቴን ፤ እግሬን ፤ አንገቴን ደረቴን ፤ ጀርባየን ፤ ብየ በስተመጨረሻም ተነከርኩበት የውሀው ቅዝቃዜ እትት ቢያስብለኝም ።
ከታጠብኩ በኋላ ከሰውነቴ የማላውቀው ግን የተጣበቀብኝ ስታጠብ የለቀቀኝ ነገር ያለ ያህል ተሰምቶኛል።
የወፎቹ ዜማ አልፎ የጠዋት ጮራ በመስኮቴ ጭላንጭል ትታየኛለች ።
ልብሴን አጥልቄ ጫማየን ተጫምቸ
በሬን ከፈትኩ ። በተረጋጋ መንፈስ ባረፍድም መጓዝ ወደፈለኩበት አቅጣጫ ጉዞየን ሀ ብየ ጀመርኩ ።
Telegram
Join
https://t.me/habesha_negn_1
241 viewstsedi, edited 04:39