Get Mystery Box with random crypto!

Zebidar Tube (ዘቢዳር)

የቴሌግራም ቻናል አርማ guragez — Zebidar Tube (ዘቢዳር) Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ guragez — Zebidar Tube (ዘቢዳር)
የሰርጥ አድራሻ: @guragez
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.29K
የሰርጥ መግለጫ

# ይህ የዘቢዳር ቻናል የሀገራችን ብሎም የጉራጌ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካ፣ ኪነ ጥበብ፣ ታሪክ፣ ርዕዮት እና ሁለንተናዊ መልክ የሚዳሰስበት የመገናኛ የመወያያ እና የመጦመርያ አውድ ነው!

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-07-05 10:53:57 -----------------
#የበለጠ መረጃ ለማግኘት


Telegram;-     https://t.me/gurageZ

YouTube;-       https://youtube.com/channelUCspMeuO6nhHHOHZpVA1ZSSQ

Facebook;- www.facebook.com/Zebidar-Tube-100279201799689/

tiktok;- tiktok.com/@zebedir
543 viewsZebidar Tube (ዘቢዳር), 07:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 19:19:38
#የሸኔ ቡድን በምዕራብ ወለጋ በዜጎች ላይ አደጋ አደረሰ::

#በኦሮሚያ ክልል፣ ቄለም ወለጋ ውስጥ የሚገኙ ዜጎች ጭፍጨፋ ተፈጽሞባቸዋል።

@ጠቅላይ ሚኒስቲር ዐቢይ አህመድ

-----------------
#የበለጠ መረጃ ለማግኘት


Telegram;-     https://t.me/gurageZ

YouTube;-       https://youtube.com/channelUCspMeuO6nhHHOHZpVA1ZSSQ

Facebook;- www.facebook.com/Zebidar-Tube-100279201799689/

tiktok;- tiktok.com/@zebedir
1.2K viewsZebidar Tube (ዘቢዳር), 16:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 08:26:06
#የኢዜማ  አንደኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ  ፕርፌሰር ብርሀኑ ነጋን የፓርቲው መሪ አድርጎ መረጠ።

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) አንደኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ትናንት ሰኔ 26 ቀን 2014 ዓ.ም ባደረገው ምርጫ ፕ/ር ብርሀኑ ነጋን  እና አርክቴክት ዮሐንስ መኮንንንየኢዜማ መሪ እና ምክትል መሪ አድርጎ መርጧል፡፡

በተጨማሪም ዶ/ር ጫኔ ከበደን እና  ዶ/ር አማኑኤል ኤርሞን የኢዜማ ሊቀመንበር እና ምክትል ሊቀመንበር አድርጎ መርጧል፡፡

-----------------
#የበለጠ መረጃ ለማግኘት


Telegram;-     https://t.me/gurageZ

YouTube;-       https://youtube.com/channelUCspMeuO6nhHHOHZpVA1ZSSQ

Facebook;- www.facebook.com/Zebidar-Tube-100279201799689/

tiktok;- tiktok.com/@zebedir
620 viewsZebidar Tube (ዘቢዳር), 05:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 10:21:53
679 viewsZebidar Tube (ዘቢዳር), 07:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 10:21:52 #የፀጋዬ ወንድወሰን (ጋዜጠኛ) የጉዞ ማስታወሻ

ዛሬ ሰኔ 26 የክረምት ወቅት በይፋ ገብቷል ፤ ወቅቱ እስከመስከረም 25 ይቆያል ። በኢትዮጵያ የቀን ቀመር መሰረት ።

ክረምት ሲገባ ደርሶ የሚታየኝ መስቀል ነዉ፤ የመስቀል በዓል በጉራጌ ።

ፈጣሪ ይመስገን ኑሮም ከመናሩ ዘይትም ከመወደዱ በፊት ነዉ ባለፈዉ አመት በጉራጌ ዞን የመገኘቱ እድል የገጠመኝ እናም በዚያ የአመት በጀቴን የዘጋሁት ።

እንደአሁኑ የኑሮ ግለት የአመት ያልኩት በጀት ብዙ አመታታን ያሻግረኛል ፤ ያስቀረሁትን ቪዲዮ ስንቅ ማድረጌም አይቀርም።

እኔና ጓደኞቼ አዲስ አበባ ስንበላ የቆየነዉ ስጋ የቀመስነዉም ቅቤ High Copy መሆኑን ያረጋገጥነዉ ጉራጌ እንደደረስን ነዉ ።

ስጋን በአይነቱ በላነዉ  ፣  ቅቤም ጠጣነዉ  ብል ማጋነን አይሆንም ።

ልክ እግራችን እዚያ ዉብ ጎጆ በደረሰ ጊዜ የአዲስ አበባን የምግብ High copy  በአታካና ነዉ  መበቀል የጀመርነዉ ።

ጣዕሙ ዛሬም ድረስ ከምላሴ ስላልጠፋ ፆም እንዳያስፈታኝ ደጋግሜ እሰጋለሁ

አታካና - አይብ እና ቅቤ ጋብቻ ፈፅመዉ ጎጇቸዉን በአፍና ምላስና ጥርሳችሁ ቀልሰዉ ማደሪያን ጨጓራችሁ ላይ  አድርገዉ ፈልሰስ ለማለት ከጣባዉ ላይ በጉጉት የሚጠብቋችሁ የምግብ አይነት ነዉ።

አሰራሩ'ን ትንሽ ለማስረዳት ያህል  :- //ከኑሮ ዉድነቱ አንፃር ስለማይቻል  ትቼዋለሁ //

ከአታካናዉ በኋላ ግን - እርጎዉ ይመጣል ...ሳ....አብ ታደርጉታላችሁ አቤት ቅዝቃዜ ፣ ጨጓራችሁን ይበርደዋል እንደእኛ በአዲስአበባ በስጨት ብላችሁ ከሄዳችሁ '' ችስስ '' ሲል ይሰማችኋል  

  / ኡፏ ጠገብኩ ስትሉ   ደሞ መሸት ሲል ጥብሱ ይመጣል  ከዚያ  ክትፎዉ ከነቆጮዉ በኮባ ቅጠል ተዉቦ  / ...

ከዛ መነጫነጭ ትጀምራላችሁ " እንዴ ይሄ መጀመሪያ ፣ ኧረ ይሄ ይቅደም እያላችሁ ግራ እጃችሁ ከቀኝ እጃችሁ ጋር ጠብ ይገጥማል / ማን ይገላግል?

ወደቀልባችሁ ትመለሱና .... ድጋሚ ስለማይገኝ ሆድን እያሹ  መብላት ነዉ ።
እኛ ኢትዮጵያዊያን ደሞ  ነገን ስለምንፈራ አጋጣሚዎችን ደህና አደርገን መጠቀም እናዉቅበታለን።

አንዱ ይነሳና '' የበላና የተማረ ወድቆ አይወድቅም ፣ ትምህርቱን ተምረሀል ምግቡ ይቀርሀል ያዝ ብሎ የወኔ ወኔ ይሰጣችኋል ''

ያኔ  አገጫችንን ወለም ካላለን መብላት አናቆምም   ።

ከዚያ ደግሞ አለ ጨዋታዉ  ሳቁ ፣  ምርቃቱ ....ብዙ ብዙ ነገሮቹ አካባቢዉ መብራት ያልገባለት ቢሆንም የገባንበት ቤተሰብ ፍቅር ዳተኛዉን መብራት ሀይል ያስረሳናል ።

ግን ለአዲስ አበባ ቅርብ የሆነችዉን ዞን መብራት እንዴት እስካሁን ሳይገባ ቀረ ?  የተወሰኑ ቦታዎች ላይ እንቅስቃሴዎች ቢኖሩም ደካማ መሆኑን ግን ታዝቤያለሁ ። ብቻ  እኛ ሶስት ቀናትን እንደዚህ ቆይተናል ።

በርካታ ገጠራማ አካባቢዎችን ስመለከት ልጅ ሳለን በየመንደሩ የነበሩ ትልልቅ እናቶችን ያስታዉሱኛል ።

ህፃን ፣  ወጣት ፣  አዛዉንቱ ሁሉ እንደነዚያ ለልጅነቴ ድምቀት እንደሆኑት እናቶች ያሉ ናቸዉ ፤ ፍቅር ናቸዉ ። ፍቅር መግለጫዉ ብዙም አይደል እነርሱም እንደዚያዉ ።

ወደአለም ቀረብኩ ያለችዉ አዲስአበባ ግን እነዚያን እናቶች ደብቃብናለች  ወይም ጠልተዋት በየገጠሩ የሄዱ አይነት  ስሜት ይሰማኛል።

አሁን ክረምት ገብቷልና ፣ መስቀል በጉራጌ መናፈቅ ይዣለሁ ። ዘንድሮ ወደጉራጌ ምድር ብሄድም ባልሄድም በዓሉ ግን ድቅን ይልብኛል ። በሌላ ምልከታዬ እስክመለስ  ኬር እንዲሉ የጉራጌ እናትና አባቶች ለሁሉም ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን ።

-----------------
#የበለጠ መረጃ ለማግኘት


Telegram;-     https://t.me/gurageZ

YouTube;-       https://youtube.com/channelUCspMeuO6nhHHOHZpVA1ZSSQ

Facebook;- www.facebook.com/Zebidar-Tube-100279201799689/

tiktok;- tiktok.com/@zebedir
642 viewsZebidar Tube (ዘቢዳር), 07:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 08:54:45

1.1K viewsJimi, 05:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 20:47:44 #የተሻሻለው የጆካ ቂጫ (የጆካ ባህላዊ አስተዳደረ ሸንጎ) ፀደቀ።

#በተለያየ ምክንያት የሰው ህይወት ሲያልፍ በየጆካ ቂጫ መሰረት የደም ካሳ  በግፍ ወይም ሙራ ደም 3መቶ ሺ በስህተት ወይም መዳራ 150 ሺ ፣በአጋጣሚ/በጥቂት ስህተት 75 ሺ ብር እንዲከፍል ተወስኗል።

#በተያያዘም በመኪና የሚጠፋ ክቡር የሰው ልጅ ህይወት በግፍ ያጠፋ (ሙራ ደም) 2መቶ ሺ በስህተት 1መቶ ሺ ፣በአጋጣሚ 50 ሺና የአካል ማጉደል ሙሉ የህክምና ወጪ ሸፍኖ ቅጣቶች እንደየሁነታዉ የሚቀጣ ይሆናል።

#የአባላዘር ማበላሸት በተመለከተ የወንድም ሆነ የሴት አባላዘር ሆን  ብሎ ያበላሸ መሆኑ ከታወቀ በሆስፒታል እና በሃኪም ከተረጋገጠ በብር  2መቶ ሺ መቀጣት እንዳለበት ተገልጿል።

#የመግድል ሙከራ ያደረገ ወይም የሰነዘረ (የቁም ደም) በብር 1መቶሺ ብር ይቀጣ ተብሏል በቂጫው።

#በግፍ ቤት ያቃጠለ 2መቶ ሺ፣ በስህተት         1መቶ ሺ፣ በፍጹም ስህተት  50 ሺ ሆኖም የቤት ውስጥ ቁሳቁስ ከተቃጠለ ከመርፌ እስከ ትልቁ ንብረት ተደምሮ ይከፈል ሲል ቂጫው አስታውቋል።

#የቸግ ስራአቱ የማሻሻያው አካል ሆኗል። በዚህም የጆካ ባህላዊ አስተዳደር ሸንጎ የወንድ ቤተሰብ ለልጁ የትዳር ጓደኛ ለመጠየቅ ወደ ሴቷ ቤት የሚሄድ ሽማግሌ በቁጥር 7 ብቻ እንዲሆን የወንድ እና የሴት አጃቢ 10  ብቻ እንዲሆን ውሳኔ አስተላልፏል።

#በእለቱ ለሚፈጸመው የቸግ ስርአት አንድ በግ ወይም ፍየል ብቻ እንዲታረድ ተወስኖአል።ሆኖም  ይህ ቂጫ የጣሰ ከወንዱ ወገን 25ሺ ከሴቷ ወገን 25 ሺ በድምሩ 50 ሺ እንዲቀጣ  ተደንግጓል።

#በአሁን ሰአት የለቅሶ ስርአቱ በህብረተሰቡ ጫና አሳድራል ያለው የጆካ ባህላዊ አስተዳደረ ሸንጎ  በለቅሶ ለእንግዳ መቀበያ በሚል የእርድ ከብት እንዲሁም እንጀራ እና እሽግ ውሃ ማቅረብ በቂጫው ተወግዞ እንዳይፈጸም የተወሰነ ሲሆን እንግዳ መሸኛ በንፍሮ ቢቻ እንዲሆን በቂጫ ተቀምጧል።

#በመሆኑም ይህንን የተቀመጠውን ቂጫ የሻረ ሃዘንተኛው  በብር 50 ሺ መክፈል አለበት ተብሏል።

#በጉራጌ ብሄርረሰብ በግንባር ቀደምትነት ከሚጠቀሱ እድሜ ጠገብና ዘመን ከማይሽራቸው ቅርሶች ውስጥ አንዱ     ጀፎረ ነው።

#ይህን ለግል ጥቅሙ ቆፍሮ ጭቃ ያቦካ፣ጎርፍ ማጠራቀሚያ ጉድጓድ የቆፍረ፣አፈር ቆፍሮ ወደ ግቢ ያስገባ፣ የቆፋረው አፈር መልሶ እንዲሞላ የሚያደርግ ሲሆን ለዚህ ለሰራው ከፍተኛ ጥፋት 20 ሺ ብር ካሳ የሚከፍል ይሆናል።

#የጀፎረ መሬት አጥሩ አስገብቶ ቤት የሰራ፣ዛፍ የተከለ ንብረቱ ተወርሶ ለቀበሌ ገቢ እንዲሆን ከዚያ ተለክቶ የድንበር ድንጋይ ተተክሎ ካስረከበ በኋላ ካሳ 10ሺ መክፈል እንዳለበት ተቀምጧል።

#ሰብል ማቃጠል ወይም መንቀል በታዋቂ ባለሙያ ተገምቶ እንዲከፈል ተደርጎ በተጨማሪ የሞራል ካሳ ከ30ሺ እስከ 60ሺ እንዲከፈል ውሳኔ አስተላልፏል።

#የወግ ምስ በተመለከተ ማሻሻያ የተደረገ ሲሆን ሃላፊነቱ በአግባቡ እንዲወጣ የጆካ ሸንጎ ዉሳኔው አሳርፎአል።በዚህ መሰረት በሸማግሌ ያለቀ ጉዳይ ማጠቃለያ ለመስጠት በሳምንት ሁለት ቀን ቅዳሜና እሁድ አገልግሎት እንዲሰጥ ለሰጠዉ አገልግሎት በእያንዳንዱ ባለጉዳይ  3መቶ ብር ብቻ ይሰጠዋል።

#በጉራጌ ብሄር ተስካር ለሟችም ሆነ ለቀሪው ቤተሰብ አላስፈላጊ ወጪ ከማዉጣት በስተቀር የሚጠቅም ነገር እንደሌለ ይታመናል።ስለሆነም በቤተ እምነቶች የሚደረገው ስርአት እንዳለ ሆኖ ይህን ቂጫ በመጣስ ተስካር ያወጣ 
50 ሺ ብር  መክፈል እንዳለበት ቂጫ ያስገድደዋል ማለት ነው።

#ማንኛውም የጉራጌ ተወላጅ ራስንና ቤተ ዘመድን የሚያዋርድ ጋብቻ የሚያስከለክል ያልሆነ እና ያልተደረገ መጥፎ ነገር በመጥራት ለምሳሌ ኦዘ (ኦዛይ) /ዘረ ቢስ በማለት የተሳደበ መሆኑን በማስረጃ እና በሽማግሌዎች ከተረጋገጠ በኋላ 1ዐሺ ብር እንዲቀጣ በቂጫ ተቀምጧል።    

#የጆካ ቂጫ በመተላለፍ በቸግ፣በለቅሶ፣በጀፎረና በመሳሰሉት ከቅጣት የተገኘ ገቢ 50 ፐርሰንቱ ለጆካ ባሀላዊ ሸንጎ፣50 ፐርሰንቱ ለየወረዳዉ ባህል ሸንጎ በደረሰኝ ገቢ ይደረግ ያለው የጆካ ባህላዊ አስተዳደረ ሸንጎ ይህን ጉዳይ ለማስፈጸም ተባባሪ አካላት የየወረዳ እና ከተማ አስተዳደር ባህል ቱሪዝም ጸ/ቤት፣ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት፣የቀበሌ አስተዳዳር እንዲሁም እንደቀበሌዉ ብዛት የሚዋቀር ይሆናል።
ለተጨማሪ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ



#ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ የአዲስ አበባ  ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ፣ አምቦ ዩኒቨርሲቲ እና ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በመጀመርያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ያስተማሯቸው ተማሪዎች ዛሬ አስመርቀዋል፡፡

-----------------
#የበለጠ መረጃ ለማግኘት

#Share #like #Subscribe
ዩቲዩብ

https://www.youtube.com/channel/UCspMeuO6nhHHOHZpVA1ZSSQ

የቴሌግራም ቻናልም https://t.me/gurageZ

በፌስቡክ ገጻችን Zebidar Tube/ ዘቢዳር ቲዩብ
ይወዳጁን!
1.2K viewsZebidar Tube (ዘቢዳር), 17:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 20:03:48
ገጸ-በረከት #ከያዶት_የምግብ_ኮምፕሌክስ

#100_መጻሕፍት

ያዶት የምግብ ኮምፕሌክስ 100 መጻሕፍትን ለእምድብር ቤተ-መጻሕፍት ድጋፍ አድርጓል።

ድርጅቱ በሚገኝበት አካባቢ ለማሕበረሰቡ ኢኮኖሚያዊ እና ማሕበራዊ ድጋፍና እገዛ እያደረገ ይገኛል።

በየዓመቱ ለ 20 አቅመ ደካማ ተማሪዎች የደብተር እና እስክሪብቶ በመስጠት የሚያስተምራቸው ተማሪዎችም አሉ።

የድርጅቱ ባለቤት የሆኑት አቶ አበጀ ሳሕሌ፤ በድርጅቱ "#ያዶት_የምግብ_ኮምፕሌክስ ስም"በዛሬው ዕለት 100 መጻሕፍት አበርክተዋል።

Lij Abeje Sahle በማሕበራዊ አገልግሎቶች ውስጥ የማናጣው ወንድማችን ነው። እጅግ በጣም እናመሰግናለን!

ሌሎቻችሁም ሊጠናቀቅ ቀናት ብቻ የቀሩትን መጻሕፍትን የማሰባሰብ ዘመቻ ተቀላቀሉ!

ለተጨማሪ መረጃ

0983292026
0919334450
0912241972
0905604965

ከላይ በተመለከቱት ስልክ ቁጥሮች በመደወል ማስረከብ ትችላላችሁ።

በአካል ቢሮ መምጣት ለምትፈልጉ

ሱማሌ ተራ ፋቲያን የገበያ ማዕከል ሕንፃ 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 603

ልደታ አሕመድ የገበያ ማዕከል 3ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 318
162 viewsZebidar Tube (ዘቢዳር), 17:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ