2022-09-24 16:20:11
ሙፍቲ ተብዬ መሰከሩ➩➪➩➪➩➪➩➩➧
وَشَهِدَ شَاهِدٌ مِّنْ أَهْلِهَا ከኢኽዋንዮች እስከ ሱፍዮች ሙፍቲ እያሉ የሚያራግቡላቸው {ራሳቸውም ቢሆኑ ተቀዳሚ ሙፍቲ ነኝ ከኔ በፊት ሙፍቲ የለም ነበር እያለ ራሳቸውን የሚቆልሉት} ሀጂ ዑመር ኢድሪስ [ዑመር ገነቴ] ሀዳሁሏህ መውሊድን በተመለከተ ሀቁን መስክረዋል። ሙፍቲ ተብየው ትክክለኛውን ሲናገሩ እንዲህ ይላል፦
"ነብያችን የተወደሉበትን ቀን ኑብዋ የተሰጡበትን ቀን ከመካ ወደ መዲና የሄዱበትን አክብረውታል። ያከበሩትም በፆም ነው። ሰኞ ሰኞ ይፆሙ ነበር። የተወለዱትም ሰኞ ነው በአሶሁ ቀውል እእእ ነብዋ ሪሳላምም የተረከቡት ሰኞ ነው የተላኩት ሂጅራም የሄዱት ሰኞ ነው የሞቱትም ሰኞ ነው። ስለዝህ ይፆሙት ነበር ለምን ትፆማላችሁ ሰኞን ቢላቸው... የተወለድኩበት ቀን ነው ብለዋል። ሀቂቀተሱንናው [ትክክለኛውን ሱና] የፈለገ ሰው የነብያችንን ስራ መከተል የፈለገ ሰው ሰኞ ሰኞ መፆም ነው። መሰባሰብ ማብላት መጠጣት ሳይሆን ሀቂቃ [ትክክለኛ] ሱናው ሰኞ መፆም ነው። ትክክለኛው ሱና እሳቸውን መከተል መፆም ነው።"
ከራሳቸው አንደበት ለመስማት https://t.me/AbuImranAselefy/3922
ሙፍቲ ተብየው ትክክለኛ ምስክርነትን ሰጥተዋል። "ምስክርነትም በራስ በቃ" አንድ ሰው ጤነኛ እስከሆነ ድረስ እንዲህ አድርጊያለሁ ብሎ በራሱ ላይ ቢመሰክር ሌላ መረጃ ማገላበጥ አያስፈልግም የራሱ ምስክርነት በቂ ነው። ሙፍቲ ሀጂ ዑመር ኢድሪስም መውሊድ አክባሪ ከመሆናቸው ጋር ትክክለኛ ሱና እንዳልሆነ እንዲሁም ትክክለኛው ሱና መፆም እንደሆነ በሚገባ አስረድተውናል።
➲
ሙፍቲ ተብየው ስለ ሰኞ ቀን አንዳንድ ነገር ካወሩ ቡኋላ ነብያችንም ሰኞን እንደፆሙ ከተናገሩ ቡኃላ የሚከተለውን ብለዋል፦"ሀቂቀተሱንናው [ትክክለኛውን ሱና] የፈለገ ሰው የነብያችንን ስራ መከተል የፈለገ ሰው ሰኞ ሰኞ መፆም ነው።" ይላሉ
መስማት ማመን ነው
https://t.me/AbuImranAselefy/3922
ትክክለኛ አባባል ነው። መፍቲው ስላሉት ሳይሆን መረጃ ቁርአን ሀዲስ የሚደግፈው ትክክለኛ አባባል ስለሆነ ትክክል ነው። ትክክለኛው ሱንና መፆም ከሆነ እባካችሁ እናንተም ፁሙ! እኛ ሰለፍዮች ትክክለኛ ሱናን መከተል ስለምንፈልግ ከቻልን እንፆማለን። መፍቲ እንዳሉት ትክክለኛ ሱንና የፈለገ ሰው ይፁም። ከዚህ ውጭ የፈለገ ትክክለኛ ሱናን አልፈለገም። መውሊድ ብሎ መብላት መጠጣት ሱና ሳይሆን ቢድዓ ነው። ቀጥለውም ሙፍቲው እንዲህ ሲሉ ሀቋን ይናገራሉ፦"መሰባሰብ ማብላት መጠጣት ሳይሆን ሀቂቃ [ትክክለኛ] ሱናው ሰኞ መፆም ነው። ትክክለኛው ሱና እሳቸውን መከተል መፆም ነው።" ይላሉ
ከሙፍቲው አንደበት ይስሙ
https://t.me/AbuImranAselefy/3922
ጎበዝ ነዎት ሙፍቲ አላህ ሀቅን እንዲናገሩ አድርጎዎታል። አላህ አቅላችሁን አሰርቶ በምላሳችሁ ወደምትናገሩት ሀቅ በተግባርም ያስገባችሁ እንላለን። ሲቀጥል መፆም ሲገባቸው በመብላት በመጠጣት የሚያሳልፉ ሰዎችን ይምከሩ ስንል እናሳስባለን። ትክክለኛው ሱና እሳቸውን (ነብዩን) መከተል መፆም ከሆነ መውሊድ ብሎ መጨፈር ሱንና አይደለም። መፆም ሲገባችሁ በተቃራኒው መብላታችሁና መጠጣታችሁ ሱናውን መቃረናችሁን በግልፅ ያሳያል።
እኛ ደጋግመን እንዲህ እንላለን፦ ትክክለኛውን ሱና የፈለገ ሰው የነብያችንን ስራ መከተል የፈለገ ሰው ሰኞ ሰኞ መፆም ነው። ትክክለኛውን ሱንና ያልፈለገ መልዕክተኛውን መቃረን የፈለገ ደግሞ መውሊድ ያክብር!!!
ሱንናው መሰባሰብ ማብላት መጠጣት ሳይሆን ሀቂቃ [ትክክለኛ] ሱናው ሰኞ መፆም ነው። ስለዚህ ሰኞ ቀን በአመትም ይሁን በወርም ይሁን በሳምንት መብላት መጠጣት ሳይሆን መፆም ትክክለኛ ሱና ነውና እንፁም። ከበላን ከጠጣን ትክክለኛውን ሱንና ትተን ወደ ጥመት {ነብያችን ወደመቃረን} እየሄድን ነውና እንጠንቀቅ!!! ትክክለኛው ሱና ነብዩን መከተል መፆም ነው። ስለዚህ ነብዩን መከተል ከፈለጋችሁ ፁሙ! ነብዩን መከተል አልፈልግም አልፆምም እንዳውም እበላለሁ እጠጣለሁ ካላችሁ ግፉበት። ከዛ የአላህ ፍርድ ይጠብቃችኋል።
فَلْيَحْذَرِ الَّذِينَ يُخَالِفُونَ عَنْ أَمْرِهِ أَن تُصِيبَهُمْ فِتْنَةٌ أَوْ يُصِيبَهُمْ عَذَابٌ أَلِيم
እነዚያም ትዕዛዙን የሚጥሱ መከራ እንዳትደርስባቸው ወይም አሳማሚ ቅጣት እንዳያገኛቸው ይጠንቀቁ፡፡ [ሱረት አል-ኑር፣ - 63]
እነዚህን መልዕክቶች ስናስተላልፍ እናንተ የነብዩ ጠላት የሸይጧን ጓደኞች እያላችሁ የምትለፈልፉ ከሆነ መጀመሪያ መፍቲያችሁን የነብዩ ጠላት በሉ እሳቸውን ለእኛ የምትሉትን ሁሉ አሸክሟቸው ምክንያቱም ይህንን ሀቅ በሚገርም ሁኔታ መስክረዋልና። ግን አታደርጉትም ለራስ ሲቆርሱ አያሳንሱ አይነት ፈሊጥ መመሪያችሁ ስለሆነ የራሳችሁን ሰው መቆለል እና መቀደስ እንጂ መንቀፍ አታውቁም!!!
ጌታችን ሀቁን በራሳችሁ ሙፍቲ እንዲነገር ያደረገው አላህ ምስጋና ይገባው አልሃምዱሊላህ አቡ ዒምራን ሙሐመድ መኮንን
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
91 views13:20