2022-08-27 20:34:30
አስደናቂው #ለማኝ እና የባለታሪኩ ገጠመኝ
በመንገድ ላይ በመጓዝ ላይ ሳለ፣ አንድ ምስኪን ለማኝ የሚሰራው ድርጊት ላይ አይኑ አረፈ። ትኩረቱን ሰጥቶ መከታተሉን ቀጠለ። ለማኙ እንዲህ ነበር የሚያደርገው.... መጥቶ ሰደቃ የሚሰጠው ሰው ጋር ረዘም ያለ ንግግር ያደርጋል። ሁሉም ሰው ሰደቃ ሊሰጠው በመጣ ቁጥር፣ እንደ ሌሎቹ ሳይሆን ረዘም ያለ ጊዜን ያናግራል። እሩቅ ላይ ስለነበሩ የሚሉትን ነገር ለመስማት አልቻለም። በመሆኑም ጠጋ ብሎ ሰደቃ በመስጠት የሚናገረውን ነገር ለማዳመጥ ወሰነ።
ኪሱ ውስጥ የነበረው 50ብር ብቻ ነበር። ታድያ 10ብር ሰጥቼ በዛውም 40ብቅ እስኪመልስልኝ ሰፊ ግዜን ወስጄ አዳምጣለሁ በማለት፤ ሄዶ ያሰበውን አደረገ። 50ብር ሰጠውና 40ብር መልስልኝ አለው። ለማኙም እንዲህ አለው........ "ያንተ ብር የሚሆነው ይህ ወደ ኪስህ የመለስከው 40ብር ሳይሆን ለእኔ የሰጠኀኝ 10ብር ነው። ምክንያቱም ይህንን 40ብር የምታውለው ምናልባት ለዱንያዊ ጥቅም ይሆናል። ጥቅሙም እዚሁ ዱንያ ላይ ይቀራል። ነገር ግን ለእኔ የሰጠኀኝ ብር ወደ አኼራ ካዝናህ ተዘዋውሯል "....
ንግግሩ ውስጤን ስለነካው በቃ እሺ መልስ አልፈልግም አልኩት። "አይይይ እኔ አንተ ብር እንድትሰጠኝ ብዬ አይደለም ይህንን የነገርኩህ። ቀሪውን 40ብር ለኔ ሳይሆን ሌላ እኔን ለመሰለ አልያም ከእኔ ለባሰ ምስኪን ለግሰው" ሲል በድጋሚ ልቤን የሚነካ ንግግር ተናገረ። ያለኝን ለመፈፀም ልጓዝ ዞር ስል እንደገና ወደ ኋላ ጠራኝ። እኔም አቤት ብዬ በደስታ ተመለስኩ። እንዲህ አለኝ "ሌላ ንግግር ጀምረን ዋናውን ጉዳይ ረሳሁት። የብርህ ምንጭ ምንድነው?" ሲል ጠየቀኝ። እኔም ሃላል እንደሆነ በደንብ አስረዳሁት። እሱም"እንደዛ ከሆነ ማሻ አላህ!! ብርህ ምንጩ ሃራም ቢሆን ኖሮ አልቀበልህም ነበር። ወላሂ የሚመለከተኝ አላህ ምስክሬ ነው። ከማንም ሰው የብሩን ሃላል መሆን ሳላረጋግጥ ተቀብዬ አላውቅም። ሃራም ከሆነ የሰጠኝ የብር መጠን የፈለገ ቢበዛ መልስልምታለሁ" እንዲህ እያወራን የዝሁር አዛን ወጣ። እሱም አንስቼው ዊልቸሩ ላይ እንዳስቀምጠው ነገረኝ። የዙሁር ሰዓት ብዙ ሰው ከስራ ስለሚወጣ ለልመና አመቺ ሰዓት ነው። ነገር ግን እሱ ሰላቱን በማስቀደም ለአላህ እጁን ሰጠ። ወደ መስጅድ እየገፋሁኝ ወሰድኩት። እናንተ እግር፣ እጅ፣አይን እያላችሁ ሰላተል ጀመዓ የሚያመልጣችሁ ወንዶች ከዚህ ሰውዬ የት አላችሁ!!? አንቺም ሙሰልሰል እየተመለከትሽ ሰላት የሚያልፍሽ፣ቻት ላይ ተጥደሽ ወቅቱን የምታሳልፊ እህቴ ወንድሜ ከዚህ ለማኝ አንፃር አላህ ምን ይለን ይሆን!!?
ከዓመታት በኋላ ይህንን ሰው ከቦታው ላይ አጣሁት። በአካባቢው የሚገኙ ሰዎችን ስለ እሱ እንዲነግሩኝ ጠየኳቸሁ። እነሱም እርሱ ልመናውን ትቶ። ከውጭ ሀገር በመጡ #በጎ_ፍቃደኞች እግሩን ታክሞ ድኖ፣ልመና ከመተዉም አልፎ ውጭ ሀገር ሄዶ ባካበተው ሃብት አማካኝነት ትልቅ ደካሞችንና ህፃናትን የሚረዳ ተቋም ማቋቋሙን ነገሩኝ። እኔም በአላህ ስራ ተደንቄ ከዚያን ቀን ጀምሮ በቀን ሰደቃ ሳልሰጥ ውዬ አላውቅም።
ሁላችንም ዛሬ፣አልያም ይህን ሳምንተ በየቀኑ ከ5ብር በማንሳት እስከ 1ብር ሰደቃ በመስጠት ለሰባት ተከታታይ ቀናት ታላቅ አጅርን እናግኝ!!
"#ውሃ እሳትን እንደምታበርደው ሁሉ #ሰደቃ የአላህን ቁጣ ታበርዳለች" ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) አላህ በብዙ ነገር ሊቆጣብን ይችላል። ይህን ሃያል የጌቴችን ቁጣ ሰደቃ በመስጠት እናብርደው።
ይህንን ፅሁፍ #ሼር በማድረግ የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ!!
ሼር ሼር ሼር ሼር
https://t.me/al_wedud_jema
75 views{^Sala^}, 17:34