2022-07-27 12:08:21
2ቱ የኢየሱስ አገልግሎቶች
ጌታ ኢየሱስ ሁለት አይነት አገልግሎቶች አሉት። የመጀመሪያው #በምድር የነበረው #አገልግሎት (Earthly Ministry) ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ #ሰማያዊ #አገልግሎቱ (Heavenly Ministry) ነው።
• በምድር የነበረው አገልግሎቱ አስቀድሞ በትንቢት የተነገረ ነው!. (ኢሳ 61፥1) ሰማያዊ አገልግሎቱ ምስጢራዊ የነበረ ነው!. (ኤፌ 3፥3)
• በምድር የነበረው አገልግሎቱ በአራቱ ወንጌላውያን ተመዝግቧል!. ሰማያዊ አገልግሎቱ በጳውሎስ መልእክታት በመገለጥ ተገልጧል!. (ገላትያ 1፥11_12)
• ምድራዊ አገልግሎቱ በሕግ መግቦት (Dispensation of Law) ስር ነበረ። (ሮሜ 15፥9 ማቴ 5፥17) ሰማያዊ አገልግሎቱ (አሁን ያለው) የጸጋ መግቦት (Dispensation of Grace) ነው!. (ኤፌ. 3፥3_9)
• በምድር ሳለ የሰበከው የመንግሥት ወንጌል ይባላል። (ማቴ 4፥23) ወደ ሰማይ ከተመለሰ በኋላ በጳውሎስ በኩል የሰበከው ወንጌል ደግሞ የጸጋ ወንጌል ነው! (ሐዋ. ሥራ 20፥24)
• በምድራዊ አገልግሎቱ 12 ሐዋርያትን ወደ እስራኤላውያን ላከ። (ማቴ 10፥5_6 ማቴ 28፥19) በሰማያዊ አገልግሎቱ ጳውሎስን ወደ አሕዛብ ላከ። (ሮሜ 11፥13)
• የምድራዊ አገልግሎቱ ተደራሲዎች አይሁድ ነበሩ። ለእነርሱ የተሰበከው ኢየሱስ ንጉሥ፣ ነቢይ እና ሊቀ ካህናት ተብሎ ነው። (ሐዋ 3፥23 ዕብ 8፥1_2 ዮሐ 1፥50) በሰማያዊ አገልግሎቱ የቤተክርስቲያን ራስ ተደርጎ ነው የተሰበከው። (ኤፌሶን 1፥22_23)
• የምድራዊ አገልግሎቱ ተልዕኮ ወደ አይሁድ የነበረ ሲሆን ታላቁ ተልዕኮ (Great Commission) ይባላል!. (ማቴ 28፥19) የሰማያዊ አገልግሎቱ ተልዕኮ ደግሞ የጸጋ ተልዕኮ (Grace Commission) ይባላል!. (ኤፌሶን 3፥9 2ኛ ቆሮንቶስ 5፥18_20)
• ምድራዊ አገልግሎቱ በእስራኤል መቆረጥ የተዘጋ ሲሆን ወደፊት ኢየሱስ ለአይሁድ ዳግም ሲመጣ ይፈጸማል!. (ሐዋ 1፥9_11) የሰማያዊ አገልግሎቱ ማጠቃለያ የክርስቶስ አካል (የእኛ) መነጠቅ (Rapture) ነው። (1ተሰ 4፥13_18)
በርናባስ ዘመነ
ለሌሎች ሸር አድርጉት
https://t.me/gracecom
470 viewsBarnabas Zemene, edited 09:08