ጽድቃችን በምን? በሮሜ 4:25 ላይ ኢየሱስ እኛን ስለ ማጽደቅ ከሞት እንደተነሳ የእግዚአብሔር ቃል ይናገራል። " ስለ በደላችን አልፎ የተሰጠውን እኛን ስለ ማጽደቅም የተነሣውን ጌታንችንን ኢየሱስን ከሙታን ባስነሣው ለምናምን ለእኛ ይቈጠርልን ዘንድ አለው። (ወደ ሮሜ ሰዎች 4:24-25) ሮሜ 5:9 ላይ እኛ የጸደቅነው በኢየሱስ ክርስቶስ ደም እንደ ሆነ የእግዚአብሔር ቃል ይነግረናል። " ይልቁንስ እንግዲህ አሁን በደሙ ከጸደቅን በእርሱ ከቍጣው እንድናለን።" (ወደ ሮሜ ሰዎች 5:9) ታዲያ የጸደቅነው ኢየሱስ ከሞት በመነሳቱ ነው ወይስ በደሙ ነው? በእርግጥ ይሄ ሁለቱ ሀሳብ ይጋጫሉን? የማይጋጩ ገለጻዎች ከሆኑ እንዴት እናስታርቃቸዋለን? 55 views17:57