ለሀገሬ እፀልያለሁ
ሀገራችን ኢትዮጵያ ከምንጊዜውም በላይ የእግዚአብሄርን ጣልቃ ገብነት አጥብቃ የምትፈልግበት ወቅት ላይ እንገኛለን። ግሬት ኮሚሽን ሚኒስትሪ ኢትዮጵያም ላለፉት ወራት #ለሀገሬእፀልያለሁ በሚል ርዕስ ስለኢትዮጵያ ግድ የሚላቸውን ሁሉ ለፀሎት በማስተባበር እንደዚሁም በጦርነቱ ምክንያት የተፈናቀሉ እና ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የተለያዩ ድጋፎችን በማሰባሰብ ለማገዝ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል አሁንም በማድረግ ላይ ይገኛል ።
በመሆኑም ስለሀገራችን ኢትዮጵያ ሁላችንም ካለንበት ቦታ በአንድ ልብ እና በንፁህ ሃሳብ ወደእግዚአብሄር ፊት እንቀርብ ዘንድ ዛሬ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከ ምሽቱ 12፡00 ጀምሮ
የ ኦንላይን የፀሎት መረሀግብር አዘጋጅቷል።
እርሶም ካሉብት ቦታ ሆነው ይህንን ፕሮግራም በፌስቡክ የቀጥታ ስርጭት አብረውን እንዲሳተፉ በጌታ ፍቅር ተጋብዘዋል።
ለሀገራችን ሳናቋርጥ እንፀልይ ሌሎችም እንዲፀልዩ እናበረታታ።
#ለሀገሬእፀልያለሁ #prayforEthiopia
የማህበራዊ ድረገፅ ፕሮፋይል ፒክቸራችንን በዚህ ፍሬም በመቀየር ብዙዎችን ለፀሎት እንዲነሳሱ እናግዝ።
የፌስቡክ ፕሮፋይሎን ለመቀየር https://bit.ly/prayethiopiaframe
የቴሌግራም ፕሮፋይሎን ለመቀየር https://t.me/add_frame_bot
ግሬት ኮሚሽን ሚኒስትሪ ኢትዮጵያ
የፌስቡክ ገፅ ፡https://facebook.com/gcmethiopia