ኀጢአተኛውና ጎስቋላው ሰው በክርስቶስ ፍጹም ስራ ነው የዳነው ። ከኀጢያቱ እድፈትም የነጻው ህያው ሆኖ በቀረበው መስዕዋት በክርስቶስ ደም ነው ። ተስፋቢስና በጨለማ ለነበረው ሰው ታላቅና ጽኑ ተስፋ ፣ የማይደበዝዝን ብርሃን ያገኘው በክርስቶስ ቤዝዎት ነው ። ነፍሱን በኀጢያት ገመድ ጠፍሮ ወደሞት ከሚነዳበት ከዚያ የጭንቅ ህይወት ያለአንዳች የራሱ አስተዋዕጾ እንዲያው በጸጋ ነው የዳነው ! የጠፋውን ፍለጋ የባሪያውን መልክ ይዞ ወደ ምድር የመጣው ጌታ ነው ፣ አስቀድሞ የወደደው ፣ ኀጢአተኛውን ሊያድነውም የመጣው ጌታ ነው ። ከዚያ ታላቅ ያምላክ ቁጣ ያዳነው ራሱን በባሪያም ምትክ አኑሮ የኀጢያት በደሉን ቅጣት እስከሞት በሆነ ታላቅ ስቃይ ወስዶለት ነው ። የዚያን ጎስቋላ ሰው ኃፍረት ይሸፍንለት ዘንድ በአለም አደባባይ ርቃኑን በእንጨት መስቀል ተሰንጠልጥሎ ታየለት ። ሁሉን የፈጠረ ጌታ ለደካማው ሰው ነፍስ በፈጠራቸው እጅ ዝቅ ብሎ ተሰጠ ። ፍጡራን በፈጣሪ ላይ አላገጡ አፌዙበት ፤ በክፋታቸው ሚዛን ላይ ሰፍረውት ሊገዙትና ሊሸጡት ተመኑ ። ሁሉን ስለጎስቋላው ሰው ነፍስ ታገሰ ፣ ሁሉን ስለወደዳት ነፍስ ተቀበለ ፣ ሁሉን ስለፍቅር ተሸከመው ። የዚያ ጎስቋላ ሰው ነፍስ ጽኑውና ብርቱው ተስፋዋ የአዳኟ ዳግም ምጽዓት ነው ! __ በጻድቅ ሰው ደም ከኀጢያታችን የዳንን ጎስቋሎች እኛ ነን ! #በጸጋው_ድነናል ! Have a nice Lords day ! 252 views09:19