2022-03-02 22:34:52
#የጥቁር_ህዝብ_ኩራት
#ዓድዋ_126
#ዝክረ_ዓድዋ
#የዓድዋ_ጦርነት_ዋዜማ_የኢትዮጵያ_ሁኔታ
ስለወቅቱ የኢትዮጵያ ሁኔታ ሲወሳ ኢትዮጵያ ከዘመነ መሳፍንት ተላቃ አንድነቷን ካስከበረች ገና በአሥሮቹ
ዓመታት ውስጥ እንደነበረች መጥቀሱ አስፈላጊ ነው፡፡
ይህ ጊዜ ሲጠቀስም የሕዝቡ ሥነ ባሕሪያዊ አመለካከት ከአፄ ቴዎድሮስ፣ ከአፄ ዮሐንስና ከአፄ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ጋር እንደሚያያዝ
አያጠያይቅም፡፡ የዓድዋ ዘመቻ ዋዜማ ስንል ከዘመቻው የተወሰነ ዓመት ፈቅ ብሎ ማለታችን እንደሆነ ግልጽ
ነው፡፡ በዚህ ጊዜም ሁለት ትልልቅ የኢትዮጵያ መሪዎች ያጋጥሙናል፡፡ አንደኛው በዚህ የጦርነት ዋዜማ ዋና
ከተማቸውን መቐለ ያደረጉትና እ.ኤ.አ በ1889 መተማ ላይ የተሰውት አፄ ዮሐንስ ሲሆኑ፣ ሁለተኛው ደግሞ
በ1889 የነገሡት አፄ ምኒልክ ናቸው፡፡
አፄ ዮሐንስ ጎንደር ድረስ ዘልቆ የገባውን የማህዲስቶች ጦር ለመውጋት ፊታቸውን ወደዚያው በማዞር ዘመቱ፡፡
እዚያም ሲዋጉና ድሉ ቀንቷቸው ለማሸነፍ ሲቃረቡ ቆሰሉ፡፡ ሲቆስሉም ድሉ ወደ ሽንፈት ተለወጠና በቆሰሉ
በሁለተኛው ቀን ማለትም መጋቢት 1 ቀን 1881 አረፉ፡፡ አፄ ዮሐንስ መተማ ላይ እንደሞቱ ንጉሥ ምኒልክ ንጉሠ ነገሥት ተብለው ነገሡ፡፡ ወዲውም የውጫሌ ውል ተፈረመ፡፡ ይህ ውል ግን ኢጣሊያን የኢትዮጵያ የበላይ (ፕሮቴክቶሬት) የሚያደርግ በመሆኑ በኢትዮጵያ በኩል ተቃውሞ ገጠመው፡፡
ይኼው ውል ይስተካከል ዘንድም ራስ
መኮንን ወደ ኢጣሊያ ተልከው ነበር፡፡ ይሁንና ኢትዮጵያ የውጫሌ ውል እንዲስተካከል መልዕክተኛዋን ወደ
ሮም ብትልክም፣ የኤርትራ ቅኝ ገዥ አዛዥ የነበረው ጄኔራል አንቶኒዮ ባልዴሴራ ደግሞ ከመረብ ባሻገር
ያለውን ግዛት ለመውረር ይዘጋጅ ነበር፡፡
ራስ መኮንን የውጫሌ ስምምነት በተለይም አንቀጽ 17 ትክክል አለመሆኑን ለመግለጽ ወደ ኢጣሊያ በሄዱ በወራቸው ኢጣሊያውያን፣ ‹‹ከእንግዲህ ወዲህ ኢትዮጵያ የምታደርገው የውጭ ግንኙነት በኢጣሊያ በኩል መሆን አለበት፤›› ሲል ለዓለም አስታወቀ፡፡ በዚህ ጊዜ ድሮውንም ኢትዮጵያ በኢጣሊያ እንድትያዝ ግፊት ስታደርግ የነበረችው ብሪታኒያ አስቀድማ ዕውቅና ሰጠች፡፡ የድንበር ውልም ተደራደረች፡፡ አፄ ምኒልክም እንዲህ ያለውን ውል እንደማይቀበሉት ለዓለም አስታወቁ፡፡
በዚህ ጊዜ ጦርነቱ የማይቀር ሆነና በ1887 ዓ.ም. ኢጣሊያውያን ዓድዋን ከዚያም አዲግራትን በመያዝ ወደ መቐለ ገሠገሡ፡፡ አምባላጌንም
ተቆጣሩ፡፡ እንደተቆጣጠሩም ትግራይ የኢጣሊያ ቅኝ ግዛት መሆኑን አወጁ፡፡
ይህንን የተረዱት ምኒልክ መስከረም 7 ቀን 1888 ዓ.ም. ላይ የክተት አዋጅ
አወጁ፡፡ የአፄ ምኒልክ ጦርም የመጀመሪያውን ጦርነት በአምባላጌ ላይ አደረገ፡፡ በዚህ ጦርነት ኢትዮጵያውያን ጀግንነት በተሞላበት ሁኔታ የተዋጉ ሲሆን የኢጣሊያ
ጦርም ተደመሰሰ፡፡ ከአምባላጌ በኋላም የኢትዮጵያ ጦር ችግር የገጠመው በእንዳየሱስ፣ በዕዳጋ ሐሙስና በአዲግራት በነበረው ምሽግ ነው፡፡
በዚህ ጦርነት ወቅት እንደ ራስ ስብሐት አረጋዊና ደጃዝማች ተፈራ ሐጎስ ያሉት የአጋሜ ባላባቶች ‹‹መሞት ካለብን ለእናት አገራችን ስንዋጋ እንሞታለን››
ብለው የኢጣሊያን ጦር በመክዳት ከወገኖቻቸው ጋር ሆነው እንደተዋጉ የሚታወስ ነው፡፡ በዚህም መሠረት
በኢጣሊያ የመገናኛ መስመሮች ላይ ጥቃት አድርሰዋል፡፡
በዚህ ጊዜ ጄኔራል ባራቲየሪ ከኢትዮጵያ ጦር ጋር ገጥሞ ሊያሸንፍ እንደማይችል በመረዳቱ የሰላም
ድርድር ለማድረግ ፈልጎ ነበር፡፡ ዳሩ ግን ኢጣሊያ የውጫሌ ውል ያፈረሰችውን የበላይ ጠባቂ ነኝ ባይነቷ
ልታቆም ባለመቻሏ፣ ከዚህም በላይ በያዘችው ሥፍራ ሁሉ ባንዲራዋን በመስቀሏ ውይይቱ ከጅምሩ አንስቶ
የደከመ ነበር፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ክርስፒም ጦርነቱ
እንዲቀጥል የቴሌግራም መልዕክት አስተላለፈለት፡፡ ይኼው ቴሌግራም በተላለፈ በአራተኛው ቀን የዓድዋ
ጦርነት ተካሄደ፡፡ የጦር መሣሪያና ጥይት ያለመታከት ሲገዙ የነበሩት
ምኒልክ ከኢጣሊያ ጋር የተፈጠረውን ውዝግብ በውይይት እንደማይፈቱት ሲገነዘቡ፣ በየካቲት ወር 1985 ዓ.ም. የውጫሌን ውል ማፍረሳቸውን ለዓለም
አስታወቁ፡፡
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደተጠቀሰው ሁሉ ‹‹ኢትዮጵያ ማንንም አትፈልግ እጆቿን ለእግዚአብሔር ዘርግታለች›› በማለት በኩራት አወጀች፡፡ ምኒልክም ይህን ባሉ በዓመቱ የራሳቸውን ገንዘብ አሠሩ፡፡ ከኢጣሊያ ጋር የሚደረገው ጦርነት አይቀሬ ሲሆን፣ እንደ ኢትዮጵያ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ከምትከተለው
ሩሲያ እንዲሁም በቱኒዝያና በምሥራቅ አፍሪካ ከኢጣሊያ ጋር የጥቅም ግጭት ካላት ከፈረንሣይ ጋር
ወዳጅነት መሠረቱ፡፡ ወዲያውኑም ከሩሲያ ዛር ከዳግማዊ ኒኮላስ የተላከውን ኢምባሲ በክብር ተቀበሉ፡፡
ቆይቶም በፊታውራሪ ዳምጠው ከተማና በደጃዝማች ገነሜ የሚመራ የልዑካን ቡድን ወደ ሴንት
ፒተርስበርግ ላኩ፡፡ ኢጣሊያውያን በታኅሳስ ወር 1987 ዓ.ም. የባህታ
ሐጎስን አመፅ ካከሸፉ በኋላ መረብን ተሻግረው ዓድዋ በመግባታቸው፣ ራስ መንገሻ ዮሐንስም የዚህን አፀፋ
በመመለስ መረብን ተሻግረው የኢጣሊያውያን ጠንካራ ምሽግ (ይዞታ) የነበረችውን ኩዓቲትን አጠቁ፡፡
በዚህ አድዋን ይዞ የነበረው ኤርትራ ገዥ ጀኔራል ባራቲየሪ ኩዓቲትን ለመከላከል ጦሩን አስወጣ፡፡ በጄኔራል
አርሞንዲ ጦር በመታገዝም እጅግ ከፍተኛ ውጊያ አድርጎ በጥር ወር 1988 ዓ.ም. ራስ መንገሻን
አሸነፋቸውና የትግራይ ጦር ወደ ሰንዓፌ አፈገፈገ፡፡
ኢጣሊያውያን በኩዓቲትና በሰንአፌ ያገኙትን ድልም ወደ ትግራይ ለመግባት የሚያስችለው በር
እንዲከፈትላቸው አደረገ፡፡ ይህንንም አጋጣሚ በመጠቀም ዓድዋን፣ ዓዲግራትንና መቐለን በተከታታይ
እንዲይዙ ረዳቸው፡፡
ከዚህ በኋላ ራስ መንገሻ ህንጣሎ
አጠገብ ወደምትገኘው ደብረ ሐይላ ቢያፈገፍጉም የኢጣሊያ ጦር እንደገና ድል አደረጋቸው፡፡ በዓድዋው ዘመቻ የመጀመሪያው ግጭት የተደረገው
ኢጣሊያውያን ከሰሜን ወደ ደቡብ ዘልቀው በመግባት ደርሰውበት በነበረውና የተፈጥሮ ምሽግ በሆነው
በአምባላጌ ላይ ነበር፡፡ በዚህ ጦርነት ቀጥ ያለውን ተራራ ጦራቸውን በመምራት የወጡት ጀግናው
ፊታውራሪ ገበየሁ ሲሆኑ፣ ከእሳቸው በኋላም ግራዝማች ታፈሰ ዓባይነህና ፊታውራሪ ታከለ ተከትለዋል፡፡ ከዚያም
ሌሎች የኢትዮጵያ ኃይሎች
ደርሰውላቸዋል፡፡ በጦርነቱም የኢጣሊያ ጦር ክፉኛ በመመታቱ የጦር አዛዥ ሜጀር ፒየትሮ ቶዜሊ ከሞቱት
አንዱ ሆነ፡፡
#የጥቁር_ህዝብ_ኩራት
#ዓድዋ_126
#የኢትዮጵያውያን_ድል
#VictoryofAdwa
#Ethiopia
@GOLDENTHINKING
192 viewsEyob G, edited 19:34