Get Mystery Box with random crypto!

ሰናይ ግጥም

የቴሌግራም ቻናል አርማ giximochi — ሰናይ ግጥም
የቴሌግራም ቻናል አርማ giximochi — ሰናይ ግጥም
የሰርጥ አድራሻ: @giximochi
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.48K
የሰርጥ መግለጫ

ሰው ማለት ሰው ያጣለት ለሰው የቆመ ሰው ማለት ነው 😍
✍️ Creater @Amele_Senai
ተቀላቀሉን @giximochi

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-21 07:10:11 እንክርዳድ ወይስ ስንዴ

በተስፋ መቁርጥ ተሸብቦ
በይሉኝታ አፉን ታፍኖ
ለትኩረት ነፍጎ ትኩረትን
ጡት የነከሰ ያጠባውን
የዕይገት ሪዕይ የራቀው
የልማት ውጥን የሌለው
እሱ እንክርዳድ ወይስ ስንዴ?
ያ.........የላይ ያፈራው።


ሰናይት ሲሻው

@giximochi
596 viewsSen@wiit, 04:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 07:09:20 የቡሄ እርግማን

የቡሄ ዋዜማ ህፃናቱ ሆ እያሉ ወደእኛ ቤት ቅውጥ አርጉት ክፈት በለው በሩን የጌታውን ሆ እያሉ በሩን ሲደበድቡ ቅድመ አያቴ ሰው የለም በያቸው እመዎ አለችኝ ዴግ ብዬ በሩን ከፍቼ ልጆች ሰው የለም በኃላ ብትመጡ ብዬ በሩን ዘጋውት። ልጆቹ ግን አልሄዱም
ሆያ ሆዬ ሆ እዛ ጋራ ላይ አንድ ጠጠር
እዚ ቤት ያሉት እንዳለ እድሜ ይጠር
ሲሉ አያቴም እኔም ሰማን ኧረ ኑ እኔ እሰጣቸሀለው አትርገሙኝ ኡኡኡ ስል አያትዬዎ ከዚህ በኋላ ረገሙሽ እኮ ሄደዎል ሄደዎል አለችኝ አንቺስ እድሜሽን ጨርሰሽ እኔ አንድ ፍሬ ልጅ እያልኩ ሳዝን ዎልኩ እላችኾለው

ሰናይ እለተ ሰንበት

ሰናይት ሲሻው

@giximochi
@giximochi
237 viewsSen@wiit, 04:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 17:28:31 ደብረ ታቦር

ደብረ ታቦር የታቦር ተራራ
አምላክ ተገለጠ ከቅዱሳን ጋራ
ሙሴን ከመቃብር
ኤልያስን ከብሔረ ሕያዋን
ሐዋርያትን ከእየሩሳሌም
አምላክ ክብሩን
ገለጠ በደብረ ታቦር
የታቦር ተራራ
የተመረጠ ነውና
አብ ተናገረ ሆኖ በደመና
አንድነት ሶስትነት
የተገለጠበት ለሐዋርያት
አይተው ያመኑበት
ደብረ ታቦር ድንቅ የታየበት
ሐዋርያት አዩ አንድነት ሶስትነት
አብ በደመና አለ ልጄን ስሙት
የብርሃን አምላክ ብርሃን ለበሰ የአማልክት አምላክ ክርስቶስ ነገሰ
ሊቀነቢያት ሙሴ ደግሞም ኤልያስ
አብረው ታዪ ቁመው ከክርስቶስ
አምላክ ታዬ የማይታይ የማይዳሰስ ስጋ ብቻ ነው ብለው ለሚያምኑት
አስመሠከረ በአንድነት በሶስትነት
የክርስቶስ ልብሱ እንደምነበረድ የሐዋርያትም ልባቸው ሲርድ
መሔድም ተሳናቸው መራመድ ።
ምድርን ነኩ በግንባራቸው
ምትሃት ያዪመስሏቸው
ቀና በለው አተኩረው ሲመለከቱ
ከአምላክ በቀር ሌላም አልታያቸው
ክርስቶስ ቀርቦ ሲዳስሳቸው
ነፍሳቸው ተመለሰች ወደ ቀልባቸው ።
በደብረ ታቦር ክርስቶስ ሲነጋገር
ድንቅ ታይቷል ግሩም ነገር
አምላክ ሲነግስ ክርስቶስ ሲከብር ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ። አሜን ።


<< ታቦርና አርሞንኤም በስምህ ደስ ይላቸዋል >> መዝ፹፰፥፲፪

ሰናይት ሲሻው

እንኳን ለደብረ ታቦር (ቡሄ) በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን መልካም በዓል ሴቶች ዳቦውን እየጋገራቹ ወንዶች ሆያ ሆዬ በሉ ተሰባስባቹ


@giximochi
@giximochi
844 viewsSen@wiit, 14:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-15 22:30:32 #መንገዱ_ዝግ _ነው

መንገዱ ዝግነው
ዝግ ነው ዝግ ነው !!!
ጥፋታችን ምንድነው?
መልስ የለም ዝግ ነው
መንገድ እንደ ሰው አያስቀይም
መንገድ ላይ ቁመው መንገድ የለም ።
እንደኮንትሮ ባንድ መንገድ እየዘጉ
በግድ ቋንቋዬን ልመዱ
በድርቅና ባህሌንም ውሰዱ
ያውም በመታበዬት መንገድ እየዘጉ ።
አምላክ በቃሉ በፈጠረው
ሁሉም ፍጥረታት እንዲሄዱበት በሰራው
ካለመኖር ወደመኖር ባመጣው
መንገድ የለም አሉ እሱ በፈጠረው ።
ወይ መሰንበት አማልክት አምላክ ነን አሉ
እስኪ ተመልከቱ መላእክት መስክሩ
አምላክ በከፈተው ሲዘጋ በሩ ።
ሕጻናት ዎይታቸው አየለ
የነፍሰ ጡሮች አዎላጅ የታለ
ደካሞች ጩኸታቸው ቀጠለ
ደረሰ ደረስ እኮ በዓሉ
ትልቁ መንገድ ተዘግቶብን አሉ
ማን ይከፍታል ማን ይዘጋል?
ባለቤቱ እሱ ሲፈልግ ይዘጋል
ሲፈልግ ይከፍታል ።
ሌላው ተመልካች ነው
ምንም ስራ የለው ።
ምቀኛ ቢዘጋው አምላክ ይከፍተዋል
ከሱ ሲመጣ እንጂ ለሰው ማን ያስባል ?
በእነሱ ስልጣን በነሱ ዘመን
እኛን መርጠው ተመለሱ ሲሉን
መንገድም ሰው ለዬ አወይ ክፉዘመን ።
የመኖሩ ተስፋ እንዲህ ከሆነማ
እነሡ ከተውት እኛም አንስማማ ።
ድርና ማግ መሆኑ ይሻለን ነበረ
ጥልስ ቀላል ነው ዝምድናው ከቀረ ።
በሩን ክፈት እሳት እንዳይበላህ
አምላክ ከተቆጣ አካልም አይኖርህ ።
መፎከር ይቻላል
መዝጋትም ይቻላል
ዱላም ይቻላል
ሽጉጥም መሰዘር ይቻላል
ሌላውም ይቻላል
በጣም ከባዱ እዳውን መሸከም
እዳውን መቻል እዳውን መሸከም ።
ሾላ በድፍኑ ውስጡን ለቄስ
የነ እምዬ ዘመን መቼም አይመለስ
አፈር ይቅለለው ጥሩ ለሠራው
የአሁኑ አይነሳ ሥራ ለሠሪው ።
መቃብሩ ላይ እንትከል ተክሉን
ለምለሙን ሳይሆን አጋም እሿሁን
በሕግ አምላክ ሲባሉ
ልክ ይከበር ሲባሉ
ሕግ አናውቅም አሉ
በፍርድም አደሉ
መንገዱ ዝግነው
ማን በሰራው ማን ባቆዬው?
ማን ነው አውራ ነኝ ያለው ?
እስኪ ይናገር ታሪክ ይዘክረው
ገድልም ያስታውሰው
ታሪክ ይዘግበው ።
መንጋ መደዴ
እኔ አልቻለም ሆዴ
አንበስ ተኝቶ
ቀበሮ ቀደመው ከኋላው ተነስቶ ።
የእሳት ልጅ እረመጥ
የረመጥ ልጅ አመድ
ግፍን እንደጥሩ አሜን ብሎ የሚለምድ
እንደዚህ ያለውስ ይቅር አይወለድ ።
ወላዲቱ የወላድ መካን
ወይ አለመታደል ሰው አለመሆን ።
የገበያ ግርግር ለቀጣፊ በጀው
አምላክ መፍትሔውን አብጃጀው ።
ትዕግስትም ሲበዛ ራ'ስን ይጎዳል
ለጠላት መፍትሔው ቀድሞ መከላከል ።
ጠላት ዝም ሲሉት የፈሩት ይመስላል
ካልሆነ ተመክሮ ይላካል ነበልባል ።
ተመልከቱ ሞቀ ተሟሟቀ
ይኸን ጊዜ ነበር ገበያ ላወቀ ።
ምነው በፍስለታ ተሳስተው በሉ
ምነው በዐብይ ፆም ተሳስተው ሻሩ
እንደዱር አራዊት የሰው ሥጋ በሉ ።
ዘመድ ከዘመዱ አህያ ካመዱ
መባላት ነው እንጂ አንድ ነው መንገዱ ።
በክብሩ ጽናት
በፍጹም ትዕግስት
የሕሊና ዝግጅት መውጫው ለአርነት ።


ሰናይት ሲሻው

@giximochi
@giximochi
@giximochi any question @Amele_senai
984 viewsSen@wiit, 19:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-15 22:04:53 #መንገዱ ዝግ ነው አዲስ ግጥም ዛሬ ማታ 4፡30 ላይ የማጋራቹ ይሆናል ወቅቱን ያማከለ ነው እንግዲ ተጨንቄ ፅፌዎለው ጠብቁኝ

ሰናይ ምሽት
300 viewsSen@wiit, 19:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-12 19:01:08 ትንቢቱ ይፈፀም ዘንድ

ወንበዴ ነበርኩ ቀማኛም አይገልፀኝ
የመንደሩ ሰው በባህሪዬ የጠላኝ
ቀና ብለው ላዩኝ የማራራ
እጄን መስደድ ነው ካገኘውት ጋራ
የአባቴ እንባ ረግጬ የምወጣ
ይልኛል ተመከር ችግር ሳይመጣ
መልሴም አባ በእንቁላሉ ሳልቀጣ
መቀበል ነው ያለውን ጣጣ
በማለት ከቤት ስወጣ
ሳይደግስ አይጣላ ነገር
ደም ተቃባው ከንጉሳያን ዘር
የአባቱን ዙፋን የሚወርሰው
የገደልኩት አንድያ ልጁን ነው
ምን ውስጥ ልግባ ወዬት ልሸሸግ
እረኛው የጠፋ ሆንኩኝ ብቸኛ በግ
አባባ ጋር ሄድኩኝ እየተጣደፍኩ
ይቅር ይለኝ ዘንድ ስሩ ተንበረከኩ
ልብሴ በደም ተጨማልቆል
የንጉሱ ልጅ ህይወት በእጄ ጠፍቶል
አባቴ ልብህ እንዳያዝንብኝ
ይቅር ለእግዜር አልኩት መርቀኝ
በምላሹ ፊቴን በእጆቹ እየደባሰሰ
ያንተ እንደዚ መሆን እኔ ነኝ እያለ አለቀሰ
ነጩን ቲሸርቱን አውልቆ ለእኔ አለበሰ
በደም የተነከረውን እሱ ለበሰ
አሳዳጆቼ በሩን በርግደው ገቡ
አንዴ እኔን ቀጥሎ አባቴን አዩ
ነገሩ እንዲ ነው ልጅ ባጠፋ
አባት አንገቱን ደፋ
በደም የቆሸሸውን ልብስ የለበሰው
ይሄ ነው አሉ ንጉሱን ልጅ ያሳጣው
ይሙት ይሙት ብለው ፈርዱ
በሰይፍ አንገቱን አረዱ
አይእኔ እያየ ሞተ አባቴ
የሞቱ ቀን ጀመረች ህይወቴ
የደረሰብኝ ስቃይ የመጣውት መዘዝ
ከዕለት ወደ ዕለት ሆነብኝ የሚጠዘጥዝ
የአባቴ ሱሪ ውስጥ አገኘው ወረቀት
ሳነበው ገረፈኝ እንደ ስለት
ምናልባት አልሆንኩልህም ጥሩ አባት
እዚ ቦታ እንድደርስ ክፍያለው ብዙ መስዎዕት
ባንተ መቼም ቢሆን አልደራደር
ፍቅሬን አሳይሃለው ወርጄም ቢሆን መቃብር
አንተ ግን አስብ ስለወደፊት
የቀረችህን ዕድሜ ፈጣሪህን አስብባት
በጉብዛናህ ወራት አስበኝ እንዳለው
አምላክህን መቼም እንዳታሳዝነው
ጉልበትም ይሆናል ደከማ
ይልፈሰፈሳል እንደ ቄጤማ
እንዳያልቅ በልብህ ውስጥ ያለው ሻማ
ልጅ ስትወልድ በእንቁላሉ ቅጣ
እንደ አባት ሲያሻህ ተቆጣ
አደራ ልጄ ወዳጄ!

ሰናይት ሲሻው

@giximochi
@giximochi
804 viewsSen@wiit, 16:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-06 22:47:07 የሀዘን እንጉርጉሮ

የሸክላ እቃን እሳት ይፈትነዎል
የሰውንም ገላ አፈር ይበላዎል
ወፍ ከዘመዱ ይኖራል
ሰውም ኑሮ ኑሮ ወደ አያቶቹ ይጨመራል
ዝናቡ አመረረና ብላቴናውን ወሰደ
መኖሪያ አሳጥቶ ቤተሰቡን አሰደደ
ምነው እዮባ ምነው በክረምቱ
ምነው በጨለማው ምነው በሌሊቱ
አፈር ለመሆን ምን አስቸኮለህ ቢወጣ ክረምቱ
ሞት ሆይ ሰው በደህና ሲኖር ቀምተህ የምትወስደው ላፈር
ምነው ሰውን ብታከብር ብታፍር


ባለፈው እሁድ አማኑኤል ቤተክርስቲያን አካባቢ በተፈጠረው የጎርፍ እና የመጋዘን መደርመስ አደጋ ወጣት #እዮብን አተናል በጣም አዝነናል በእውነት ብዙ ህልም ማሳካት የሚፈልገው ነገር ይኖራል ግን ህይወት እንደዚ ነው እኛ ስለፈለገን አይደለም ምንም ነገር የሚሆነው ሁላችንም መጠንቀቅ ነው ያለብንን ያለነው ክረምት ላይ ስለሆነ ዝናቡም እየከበደ ነው ስለዚህ ነቅታቹሁ ተኙ እያልኩ የወንድማችንን ነፍስ በአፀደ ገነት ያኑርልን

በእኔ እና በግጥም ቤት ስም ይሁንልኝ ሰናይት ሲሻው

@giximochi
557 viewsSen@wiit, 19:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-06 21:16:55 ቤት ተከራይቼ ነው የምኖረው እናቴ ቲቪዎን ቀይራ የድሮውን ውሰድ ብላኝ ይዤ ቤት ከገባው በኃላ አከራዬ በሩን አንኳኩ እና ስማ የእኔ ልጅ ቴሌቭዢን ነው እንዴ ይዘህ የገባህ? አዎ ማዘር ከሚደብረኝ ብዬ እኮ ከቤት አምጥቼ ነው።።።።አይ አይ ለውጥማ አለ እኔ አዝኜልህ ከየት ያማጣል ብዬ እኮ ነው ቤት ኪራይ እስከዛሬ ያልጨመርኩ በል በሚቀጥለው ወር ሶስት መቶ ብር ጨምረህ ነው የምትሰጠኝ።።።ኧረ ማዘር እናቴ ከምትጥለው ብዬ እኮ ነው ያመጣውት ደሞ ሰዎችን ግማሽ አንገታቸውን ይቆርጣቸዎል ቦርዱ መሰለኝ የተቃጠለ

Amele senai

@giximochi
470 viewsSen@wiit, 18:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-05 21:38:30 በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ

እኔ ወይስ አንተ

ክፍል አስራ ስምንት


ጣቢያ እንደደረስኩም ቃሌን ሲቀበሉ አንዳንች ነገር አልተናገርኩም መልሽልኝ ማነው የገደለው ሲል እኔ ነኝ ያረኩት ብሎ የልጄ አባት መጣ በእውነት በመምጣቱ ምንም አልተገረምኩም ይገርማል ሰው ካላረጅ እንዴት ይሞታል እኮ ለምን የእድሜው አጋማሽ ላይ ይሞታል በጣም በጣም ልብ ይሰብራል እኔ አላቻልኩም ህልም መሆን አለበት ብዬ ለመንቃት ሞከርኩ ግን ግን ላይመልስ ሄዶል "የነገ ሞች የዛሬን ሞች ይቀብራል" እንደሚባለው ማንም ከሞት አይቀርም ግን እጣ ፈንታ ነው በሰው እጅ መሞት ምን እያሰብኩ እንደሆነ መገመት አይከብድም ቆይ ፈጣሪ ሲፈጥረን የምንሞትበትን ቀን ይፅፋል? ወይስ ደግ ሰዎች ሲሞቱ እግዚአብሔር ፈልጎቸው ነው የወሰዳቸው ክፉ ሰዎችም ሲሞቱ እግዚአብሔር ተማሮባቸው ነው በለጋ እድሜያቸው የቀጫቸው የምንለው እስከመቼ ይሆን። እኔ ጩቤውን አንስቼ አልወጋውትም ግን እኔ ነኝ የገደልኩት በሚል ህሊና ዘላለሜን ታስሬ እኖራለው። የምድር እስር ቤት በጣም ቀላል ነው ግን በቁም እየኖሩ የጥፋተኝነት ስሜት ዘወትር የሚስማን ከሆነ መቼም ሊድን የማይችል ጠባሳ ሆኖ ይቀራል። ፖሊስ ጥያቄ ጀመረ ለምንድነው የገደልከው? ከሚስቴ ጋር ሲማግጥ አግኝቼው በንዴት አደረኩት አለ። ይሄ አግባብ አይደለም በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ አሉ ይሄ አይደል መሟቱ ሳያንስ እንደዚ አይነት ክስ ኧረ በጊዮርጊስ ለሰሚም ለቀባሪም የማይመች ወሬ ነው ። እሱም ወደ ማረፊያ ቤት ወሰዱት እኔ ወዴት እንደሚሄዱ አላውቅም ወደ ቤት ሄድኩኝ መንገድ ላይ ልጄ እሳት እንደተቃጠል ሲያወራ ነበር የዛሬው ቀን ለእኔ የተረገመች ቀን ትሁንልኝ እዮብ የተወለደበትን ቀን ረግሞል እኔ ይቺን እለት እንዳልቃና የተሰበርኩባት ናት እና በየአመቱ ቀኖን አስቤ ከጠዎት እስከ ማታ ምንም እህል ሳልቀምስ ጨለማ ቤት ውስጥ እራሴን ልቅጣ ብዬ ተማረርኩ። ቤት ደረስኩ አንኳኳው የሚከፍት እስኪገኝ ደጅ ጠናው በስተመጨረሻ ቤቱ ተከፈተ ዘመዳችን ናት ተመስገን አለች እያልኩኝ ከት ብላ ሳቀች ምን ያስቅሻል አልኳት መምጣትሽ ገርሞኝ ነዋ አለች እስቲ ዞር በዪ ብዬ ስገባ ልጄ የለም እንዴ ልጄስ ያብ ቃልስ እያልኩ ቀወጥኩት የውልሽ ቃል አያቱ ወስደውታል አለችኝ። ለምንድነው የወሰዱት እኔ እኮ ነኝ እናቱ ስላት ጋሼ መ'ቶ አንቺ ከማንም ዱርዬ ጋር ስትንዘላዘይ እንዳገኘሽ እና ሊገድለው ሲሞክር ጎረምሳሽን እንደገደለው ለእናቱ ደውሎ ነገራት ምናልባት የሞተው ወንድሟች ካሉት ልጄን እንዳይገሉብኝ ሲቀጠል እናቱ ይዛው እንዳጠፋ አሁኑን ኳንትራት ታክሲ ይዛ መታ እንድትወስደው ነግሮት ነበር አለች እና ተነፈሰች እኔም እና ባባ ከለለ አንቺ እዚ ቤት ምን ትሰሪያለሽ አልኳት በንዴት እኔን ቤት ጠብቂ ብለው ጋሼ አደራ ስትወኛል አለችኝ ልጄ የሚተኛበት ክፍል ገብቼ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ ከሁለት ያጣ ሆንኩኝ ምስኪን እሙ የልጄን ልብስ አቅፌ ተኛው ከባድ ቀን ስላሳለፍኩ እንቅልፍ ሳያንገራግር ነበር የወሰደኝ ። ማነው የሚቀብረው የትውልድ ሀገሩ ነው እሬሳው የሚላከው ወይ ጉዴ ብዬ በጠዎት ወደ እሱ ቤት ሄድኩኝ ፀጥ ረጭ ያለ ነበር ሁለት ባል እና ሚስት ሀኪም ቤት አብረውት እንደነበሩ አውቃለው የእነሱን ቤት አንኳኳው ሚስትዬዎ ከፈተችልኝ በጣም እንደደከማት ታስታውቃለች አይዞሽ ብላ አቀፈችኝ እና ወደ ቤት ጋበዘችኝ ለቀብር መድረስ አለብኝ እባካቹ እርዱኝ ብዬ ተማፀንኮቸው። የምደርሽ አይመስለኝም ዛሬ ሰባት ሰዓት ላይ ነው ደግሞ ወጣ ያለ ገጠር ነው እኛም ተረጋግተን ለሰልስቱ ነው የምንሄደው አለችኝ ሲሄደ ይዛኝ እንደምትሄድ ቃል ገባችልኝ ።


ይቀጥላል።።።።።።።

ሰናይት ሲሻው

@giximochi
@giximochi
478 viewsSen@wiit, 18:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-02 23:10:17 ብዙ ተስፋ ያላት ይቺ ባለ ራዕይ ሬሳዎ ወደ ሀገር ቤት ይላካል እኛም እናዝናለን ምናምን ምናምን

እውነት ተደብቃ አቀር ነገር ንፁህ ደም ነው አ የፈሰሰው።።። አከራያቸው እንዲህ ስትል ተሰማ ሰሞኑን በጣም ይጨቃጨቁ ነበር ልጅቶ ከሞተች በኋላ አንገቷ እንደተቧጫጨረ ቀይ ሆኖ እንደነበር የመጣያቸው ሰበብ ደግሞ እሱ ውሽማ እንዳለው ልጅም እንዳስረገዘ ምናምን ምናምን እሱ ያሰበው በከሰል ጭስ ሞተች ለማስባል እንደሆነ ነገር ግን እራሱ አንቆ ነው የገደላት even ለምርመራ እራሱ ሀኪም ቤት አልሄደችም እራሱ ገንዙ ነው አሉ የላካት ምስኪን


አሁን ማነው የሚታመነው?

ሰናይት ሲሻው


@giximochi
515 viewsSen@wiit, 20:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ