በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ
እኔ ወይስ አንተ
ክፍል አስራ ስምንት
ጣቢያ እንደደረስኩም ቃሌን ሲቀበሉ አንዳንች ነገር አልተናገርኩም መልሽልኝ ማነው የገደለው ሲል እኔ ነኝ ያረኩት ብሎ የልጄ አባት መጣ በእውነት በመምጣቱ ምንም አልተገረምኩም ይገርማል ሰው ካላረጅ እንዴት ይሞታል እኮ ለምን የእድሜው አጋማሽ ላይ ይሞታል በጣም በጣም ልብ ይሰብራል እኔ አላቻልኩም ህልም መሆን አለበት ብዬ ለመንቃት ሞከርኩ ግን ግን ላይመልስ ሄዶል "የነገ ሞች የዛሬን ሞች ይቀብራል" እንደሚባለው ማንም ከሞት አይቀርም ግን እጣ ፈንታ ነው በሰው እጅ መሞት ምን እያሰብኩ እንደሆነ መገመት አይከብድም ቆይ ፈጣሪ ሲፈጥረን የምንሞትበትን ቀን ይፅፋል? ወይስ ደግ ሰዎች ሲሞቱ እግዚአብሔር ፈልጎቸው ነው የወሰዳቸው ክፉ ሰዎችም ሲሞቱ እግዚአብሔር ተማሮባቸው ነው በለጋ እድሜያቸው የቀጫቸው የምንለው እስከመቼ ይሆን። እኔ ጩቤውን አንስቼ አልወጋውትም ግን እኔ ነኝ የገደልኩት በሚል ህሊና ዘላለሜን ታስሬ እኖራለው። የምድር እስር ቤት በጣም ቀላል ነው ግን በቁም እየኖሩ የጥፋተኝነት ስሜት ዘወትር የሚስማን ከሆነ መቼም ሊድን የማይችል ጠባሳ ሆኖ ይቀራል። ፖሊስ ጥያቄ ጀመረ ለምንድነው የገደልከው? ከሚስቴ ጋር ሲማግጥ አግኝቼው በንዴት አደረኩት አለ። ይሄ አግባብ አይደለም በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ አሉ ይሄ አይደል መሟቱ ሳያንስ እንደዚ አይነት ክስ ኧረ በጊዮርጊስ ለሰሚም ለቀባሪም የማይመች ወሬ ነው ። እሱም ወደ ማረፊያ ቤት ወሰዱት እኔ ወዴት እንደሚሄዱ አላውቅም ወደ ቤት ሄድኩኝ መንገድ ላይ ልጄ እሳት እንደተቃጠል ሲያወራ ነበር የዛሬው ቀን ለእኔ የተረገመች ቀን ትሁንልኝ እዮብ የተወለደበትን ቀን ረግሞል እኔ ይቺን እለት እንዳልቃና የተሰበርኩባት ናት እና በየአመቱ ቀኖን አስቤ ከጠዎት እስከ ማታ ምንም እህል ሳልቀምስ ጨለማ ቤት ውስጥ እራሴን ልቅጣ ብዬ ተማረርኩ። ቤት ደረስኩ አንኳኳው የሚከፍት እስኪገኝ ደጅ ጠናው በስተመጨረሻ ቤቱ ተከፈተ ዘመዳችን ናት ተመስገን አለች እያልኩኝ ከት ብላ ሳቀች ምን ያስቅሻል አልኳት መምጣትሽ ገርሞኝ ነዋ አለች እስቲ ዞር በዪ ብዬ ስገባ ልጄ የለም እንዴ ልጄስ ያብ ቃልስ እያልኩ ቀወጥኩት የውልሽ ቃል አያቱ ወስደውታል አለችኝ። ለምንድነው የወሰዱት እኔ እኮ ነኝ እናቱ ስላት ጋሼ መ'ቶ አንቺ ከማንም ዱርዬ ጋር ስትንዘላዘይ እንዳገኘሽ እና ሊገድለው ሲሞክር ጎረምሳሽን እንደገደለው ለእናቱ ደውሎ ነገራት ምናልባት የሞተው ወንድሟች ካሉት ልጄን እንዳይገሉብኝ ሲቀጠል እናቱ ይዛው እንዳጠፋ አሁኑን ኳንትራት ታክሲ ይዛ መታ እንድትወስደው ነግሮት ነበር አለች እና ተነፈሰች እኔም እና ባባ ከለለ አንቺ እዚ ቤት ምን ትሰሪያለሽ አልኳት በንዴት እኔን ቤት ጠብቂ ብለው ጋሼ አደራ ስትወኛል አለችኝ ልጄ የሚተኛበት ክፍል ገብቼ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ ከሁለት ያጣ ሆንኩኝ ምስኪን እሙ የልጄን ልብስ አቅፌ ተኛው ከባድ ቀን ስላሳለፍኩ እንቅልፍ ሳያንገራግር ነበር የወሰደኝ ። ማነው የሚቀብረው የትውልድ ሀገሩ ነው እሬሳው የሚላከው ወይ ጉዴ ብዬ በጠዎት ወደ እሱ ቤት ሄድኩኝ ፀጥ ረጭ ያለ ነበር ሁለት ባል እና ሚስት ሀኪም ቤት አብረውት እንደነበሩ አውቃለው የእነሱን ቤት አንኳኳው ሚስትዬዎ ከፈተችልኝ በጣም እንደደከማት ታስታውቃለች አይዞሽ ብላ አቀፈችኝ እና ወደ ቤት ጋበዘችኝ ለቀብር መድረስ አለብኝ እባካቹ እርዱኝ ብዬ ተማፀንኮቸው። የምደርሽ አይመስለኝም ዛሬ ሰባት ሰዓት ላይ ነው ደግሞ ወጣ ያለ ገጠር ነው እኛም ተረጋግተን ለሰልስቱ ነው የምንሄደው አለችኝ ሲሄደ ይዛኝ እንደምትሄድ ቃል ገባችልኝ ።
ይቀጥላል።።።።።።።
ሰናይት ሲሻው
@giximochi
@giximochi