በክረምት............ በክረምት በብርዱ፥ በናፍቆት ረመጥ፤ በሞኝ አበስብስ ውስጥ፥ ሞኝ ልቤ ሲሰምጥ፤ ከንፋስ ሽውታ፥ከመብረቅ ብልጭታ፤ በሀሣብ ትመጫለሽ፥ እንደ ድንገት ለአፍታ። በአል እስኪመጣ፥ ዘመን ተቀይሮ፤ በአጥር እስክንዘል፥በጀርባ በጓሮ፤ ደግሞ እስክንጠራ፥ ት/ቤት ቢሮ ፤ እንዴት አድርጎሻል፥በክረምቱ ኑሮ፤ ትዝ አላለሽም ወይ፥የመምህሩ እሮሮ፤ እኔ.............…......... ባይኖረኝም ፍቅር፥ለትምህርቱ ከቶ፤ ቀኑን እጠብቃለሁ፥እስኪነጋ መሽቶ፤ በጋው እስኪመጣ፥ክረምቱን ረቶ፤ እንችን እስኪያሳየኝ፥አምላኬ ራርቶ። ተፃፈ በ አቅሌስያ ፋንታሁን (@eyulka፣@akli03) 438 views18:18