2022-07-15 18:57:01
በቀጣይ አመት በ70 የትምህርት ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና እንደሚሰጥ ተገለፀ።
የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የአስተዳደርና መሠረተ-ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ሰለሞን አብረሃ (ዶ/ር) ከሚመጣው አመት ጀምሮ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና በ70 ፕሮግራሞች መሰጠት እንደሚጀምር ገልፀዋል።
ስራ አስፈፃሚው ይህን የተናገሩት የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የ2014 ዓ.ም በጀት አመት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2015ዓ.ም በጀት አመት እቅድ በቀረበበት ወቅት ነው፡፡
በጦርነቱ የወደሙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን መልሶ በማቋቋም ወደ ሥራ ማስገባት መቻሉ በ2014 በጀት አመት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ርብርብ እና ጠንካራ ትብብር የታየበት መሆኑ ተገልጿል።
በትግራይ ክልል ዩኒቨርስቲዎች ይማሩ የነበሩ እና በጦርነቱ ምክንያት የወጡ ተማሪዎችን በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ምደባ በመስጠት ትምህርታቸውን የማስቀጠል ስራ ውጤታማ እንደነበር ተጠቅሷል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ዓለም አቀፈዊ አጋርነት እየጎለበተ መምጣቱ ለቀጣይ አመት የእቅድ አፈጻጸም ስኬት በምቹ ሁኔታነት ተገምግሟል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኦድት ግኝቶችን ለመቀነስ በከፍተኛ ትኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገልጾ የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላትም የግዥ ሥርዓት መመሪያዎችን ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተጨባጭ ሁኔታና ባህሪያት በተለይም ከተማሪዎች አገልግሎትና ምርምር ሥራዎች አንጻር መልሰው ቢቃኙት ጥሩ እንደሚሆን አስተያየት ተሰጥቷል ፡፡
በቀጣይ አመት በ70 የትምህርት ፕሮግራሞች ለሚሰጠው የመውጫ ምዘና ከወዲሁ ዝግጅት እንደሚደረግ ተመላክቷል፡፡
@GhionMaleda
256 views15:57