Get Mystery Box with random crypto!

📚 የኛ_ግጥም 📚

የቴሌግራም ቻናል አርማ getamiyan — 📚 የኛ_ግጥም 📚
የቴሌግራም ቻናል አርማ getamiyan — 📚 የኛ_ግጥም 📚
የሰርጥ አድራሻ: @getamiyan
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8.07K

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-05-03 09:36:10 አንድ ሰውየ ወደ ታላቅ የሱፊ መምህር ይሄድና የገንዘብ ስጦታ ሊያበረክትላቸው እንደፈለገ ይነግራቸዋል።

እኚህ የሱፊው መምህርም ጥያቄው ከሰሙ ቡሃሏ"ብርግጥ ሀብታም ከሆንክ ስጦታህን እቀበላለሁ ደሀ ከሆንክ ግን አልቀበልምህም "ይሉታል።

ሰውየውም "በርግጥ ሀብታም መሆኔ አይጠራጠሩ"ይሏቸዋል "ሀብታም ከሆንክ እንግዲያስ ምን ያክል ገንዘብ አለህ?" ይሉታል "ሁለት ሺ ወርቅ አለኝ ብሎ "ብሎ ይመልሳል "
መምህሩም "አራት ሺ ቢሆንልህ ትመኛለህ "ይሉታል
ሰውየው"በርግጥ እመኛለሁ " ይላል "ስደስት ሺ ወርቅ ቢሆንልህስ ትመኛለህ " ይሉታል
ሰውየውም "መመኘቴ እማ አይቀርም" ይላቸዋል
እሳቸውም "አስር ሺ ቢሆንልህስ "ይሉታል
ሰውየውም "በርግጥም እመኛለሁ " በማለት መለሰ
መምህሩም እንዲህ አሉት ተመልከቱ "ስትመጣ ሀብታም ነኝ ብለሀኝ አልነበረምን ነገር ግን አንድ አንዳች የሀብት ምልክት ግን አላየሁብህም።

እንዳንተ አይነት ደሀና በዙ የሚመኝ አይቸ ስለማላውቅ ከንተ ገንዘብ መቀበሉ አግባብ መስሎ አልታየኝም ለኔ ልትሰጠኝ የመጣሀውን ገንዘብ በጉደለትህ ጨምርበት እና ደስታ አግኝ ከዛ ሀብታም ስትሆን ያኔ ትሰጠኛለህ "በለው አሰናበቱት።

ከዚህ ምንረዳው ነገር ቢኖር እውነተኛ ሀብት ገንዘብ ሳይሆን ራስህን በማሸነፍ ስሜቶችን መግድል ሲሆን አንድ ሰው ሀብታም ነው ሚባለው ደሞ ባለው ነገር ሲረካና በቃኝ ሲያውቅ ብቻ ነው።

ውብ አሁን

Semir ami
3.5K viewsسمير ايمي, 06:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-30 13:42:12 #ተነድፈሽ_ክበሪ
:
:
እኔ አልነደፍም የሚለው ፉከራ
በገዛ አንደበትሽ በኩራት ሲወራ
ካንዴም አስር ጊዜ ደርሶ ሰምቻለው
ትክክል ነው ብሎም የሚያጎበጉብ ሰው በቅርብ አይቻለው።
:
:
እውነት ነው ወይ ብዬም በዙሪያሽ ያሉትን ዞሬ ሳጤናቸው
መላከፍ ነው እንጂ መንደፍ የማይችሉ ተራ ዝንቦች ናቸው።
:
:
አፍኜው ነው እንጂ ድሮም ያንቺ ነገር ያንገበግበኛል
ከንቱ ፉጨት ከቦሽ መኩራትሽ ገርሞኛል።
:
:
ከ ዐጀቦችሽ አንፃር መደምደምሽን ሳይ አናገረኝ እንጂ የሆዴ መከፋት
ባንቺ አልተጀመረም አደባባይ ቆሞ በጀሌ ተከቦ አጉል ጉራ መንፋት።
:
:
እውነት እውነት ስልሽ ያለመነደፍሽን ሚስጥሩን ላወቀው
ልክ እንደኔ ሁሉ ሆድ ቢብሰው እንጂ ቅንጣትም አይደንቀው።
:
:
ይልቁን አንቺ ሴት አንዣባቢሽ በዝቶ እንዳትዘናጊ
የማሩን እንጀራም ያንቺ እንድታደርጊ
ተነድፎ ለመክበር በይ ከንብ ተጠጊ።

Ami
3.1K viewsسمير ايمي, 10:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-30 13:41:28
@Abrham_Teklu
2.6K viewsAbrsh, 10:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-21 17:00:03 ☞ ዝክረ ኸሚስ #6
-
መሀባ
-
አንዳንዶቻችን መሀባ ፍቅር የሁሉም ነገር ጅማሮ ፣ የመድረስ ሁሉ መነሻው እንደሆነ
ዘንግተነዋል ። እንኳን የሰው ልጅ ቀርቶ የእህል ቡሆ ‘ንኳ ለምጣድ ቢደርስም ሙሀቻው
እርሾ አይኖረውም ። " ኺትማ ድረስ ያልዘለቀ እንኳን መሀባ ቡንም ደግ አይደለም ። "
ብላናለች ሙሂቧ አቲቃችን ... መሀባ የደግ እድል በር ነው ። የሸጋ እጣ ደጃፍ ነው ፣
የእህል ውሃ መፍለቅለቂያ የዱንያ ሰታቴዋ ነው ። ተውበትን ( ንሰሃን ) ማስታወሻ ነው ።
የተጥራራ ኒያ ሸጋ ሀርፍ ፈትሎ " ያረሂም " የሚያስለፈልፍ ያብጀልኝ ደጅህን ማዜሚያ ነው ።
የጀነት መሻገሪያው መሰላልም .... መሀባ ፣ ፍቅር ።
---
.
ወቅቱን ነው አሉ ።
.
ያ የጎጋ ቅኝት ፣
በቁርበቱ ዜማ ፣
በደግ እድል በሩ ፣
በእጣው ጆሮ ግርጌ ፣
ተንጓጉቶ አንዳልነበር የገረረው ለዝቦ የጠናው ገራለት፣
ዱንያ አውታሩ ብዙ ስልት እየለወጠ ለስልሶ አዜመለት።
.
( ማነው ? አይባልም ... ! )
.
ካልሆነም ንጋቱ ፣
ካልገጠመም ምሽት ፣
ታጓጉል እሮሮ አፍታ ሳያላዝን ፣
ቀን ሰባራ ፍርዱን በመሀባ ፈጅር ይንጋልኝ እያለው፣
ሰው ብሎ ያለው ነው ... የመቸሩ ጤዛ ደጁን የበቀለው።
----
አንደዎ ሸህ ናቸው ። ደረሳቸውን ለሽንታቸው ማዳረቂያ ( ለኢስቲብራዕ ) የሚሆን ጠጠር
ድንጋይ ይዞላቸው እንዲመጣ አዘዙት አሉ ። ደረሳውም በጠጠሩ ፋንታ ትልልቅ ድንጋይ
በትክሻው ተሸክሞ መጣና ፊታቸው ላይ አስቀመጠው ። የዛኔ ሸህዮው " ኧረ አኸይ ምነው
አንተዬ ይህንን ምን ላደርገው ነው ለመቀመጫ አላልኩህ " ሲሉት « እነሸህ ላንቱ ትንሽ
ነገር እንደት ብየ ይዤ ልምጣ ! » ብሎ መለሰላቸው አሉ ። # መሀባ

አባቴም እንዲህ ሲሉ አዳምጫለሁ ። አንድ ቀን ከቁርአን ቤት ሸሆቹ ገርፈውኝ እያለቀስኩ
ቤት ገባሁ ። ምን ሆነህ ነው ? ተባልኩ ። " ሉህህን ከትክሻ ለምን አወረድክ ብለው መቱኝ "
አልኩ አቀርቅሬ ። ( ሉህ ) ከእንጨት የተሰራች መድ ቀለም እያጠቀሱ በሽንበቆ ስንጣሪ
ገላዋ ላይ ተከትቦባት ተፅፎባት ጀማሪ ልጅ አሊፍ ብሎ የሚቀራባት ማንበቢያ ናት ።
ጠፍጠፋ ሆና ከጫፍ እና ከጫፏ ተቦርቡራ ገመድ ገብቶባት ከትክሻ ትንጠለጠላለች ።
አባቴም እንዲህ አሉኝ ። « እኔ በደረስነቴ በሸሆቹ ብትር አላለቅስም ። የሸሆቹ ብትር
ያሳድጋል ። የትልቅ ሰው ቁጣ በረካ አለው ። » ካሉኝ ቡሀላ አብሯቸውቤት ለተቀመጠው
ሰው እንዲህ አሉት ። « ምን የዛሬ ልጅ አዳብ የላቸው ። እኛ ስንቀራ ሸሆቻችን ካላዋጡን
ቂረዐቱ አይያዘንም ነበር ። » ሱብሃነሏህ ... # መሀባ
----
መሀባ የሰውነት ግንዱ ዛፉ ነው ፣ ሓድራ ቅርንጫፉ ጥላው ነው ። ሓድራም ገበያ ነው
ያደባልቃል ። እንደኒያችን እንደቅዋችን የነፍስ ቀለብ የምንሸምትበት ። ሸሬታው ኸለዋ
መጅሊስ ነው ። እገሌ ተገሌ በሚል መኩራራት ሆሳ ጥላ ሓድራ ታዛውን አይዞርበትም ።
የእኔ እንዲህ ነኝ የሚል የመኮፈስ አዛ ጠለሽ ሓድራ ቀዬውን አይጥልበትም ። ሰው በመሆን
ብቻ በመርሀባ አደጌር የሚታደሙባት የፍቅር ሰርግ ያብሮነት ድግስ ነው ። ተጥራርተው
ለአቅል የሶብር ውዱእን ተጅዲድ ( እድሳት ) የሚፈጠምባት የቀልብ ወጌሻነትም ዳኢም
አሺት ነው .... መሀባ ።
.
ዛሬ ዛሬ የሓድራን ልቅና ፣ የመሀባን ደረጃ ፣ የምናይበት መልኩ ያበግናል ። « ታልደረሱ
አይደረስም ! » ቢሆንም ነገሩ ፣ ግን ክረምቱን ሳያዩት ስለወንዙ አካሄድ ያለሸርጡ ያለሃቁ
በራስ ቢሆን ግልብ የፈትዋ ኩሬ እንቀላቅልበት ማለቱን ስንሰማ ። አንዲት የዘማቾች
የሓድራ ስንኝ ድንቅ ትልብናለች በጫሌ ቀበሌ ነው ።
አርሂብ ተብሎ ደግ ሳይታደም ፣
ሓድራ አይገባም በመቀዳደም ።
-
ግደለም ሰው ማለት አያከስርም ጎበዝ ። አተረፈ አሉ ። ማን ? " ሰው ብሎ የገበየ " መገን
። .... ይቅናን ያቀናን ። መሀባም ሓድራ ነውና ቅሉ የገባያም ገድ አለውና .... ተገዱ
ሳይታገዱ የወንድም ቁናው ላይንገረበብ ቲም ያለው ሂድያ ይስጠን ። # አሚን
.
ሀቢቢ ... ረሱል ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል « አንድ ወንድሙ የሚወደውን
ነገር በማግኘቱ መደሰቱን የገለፀለት ሰው የትንሣኤ ቀን ልእልናው ከፍ ያለ አላህ
ያስደስተዋል »
« መልካምን ነገርን ትንሽ ናት ብለህ አትናቅ ።
ወንድምህን ፈታ ባለ ፊት ማግኘት ቢሆንም እንኳ » ሙስሊም ሙስሊም ወንድሙን ሲያገኝ
እሱን በማግኘቱ ብቻ
ከምንም በላይ መደሠትና ደስ መሰኘቱንም በፊቱ ላይ
ማስነበብ ይኖርበታል ። የወንድም የወዳጅ ሀቁን ስንቶቻችን እናውቀዋለን ።
-----
ያረብ
።።።።።።
በአሪፎች ቅልስ ... ከውንህ ይሞጠላል ፣
በተቅዬች ግርዶሽ ... ሀምድ ይንከባለላል ፣
ያመሰጋኝህ ግብር
መርሀባን ሲታደል ...
ቀኑን ሊደላደል - - ምንዳው ሲሞናደል ...
እዝነትህ ሲዘንበው - - በረካህ ሲጎርፈው፣
ሰው ብሎ ይተማል ነፍስያ ሳይጠልፈው።
..
ምናለ ጌትዬ ...
.
ስለሰው ብባባው ፣
ስለሰው ባነባው ፣
ነክሮኝ ብንቧችበት - - ባህሩን ብዋኝበት ...
ሰው ብሎ ሰው ሊሆን ሰውነት ካለበት ።
ምናለ ...
( እኔም በተመኔ በቀኔ ብቃና ... ! )
በገረረው ንጋት ...
ወዙ በተላሰ ድርቅና ሰንጥቆት በተፍረከረከው ፣
የሙሂቡን ኪታብ ገልጦ ካለመቅራት ...
አይኔን በገለጥከው - - ልሳኔን ባዳንከው ?!
ሓድራ መሀል ውዬ - - ሓድራ መሀል ባድር ፣
በቻልኩት ዘምቼ ፣
ከዘመኔ አልቦ ላይ - - የቀልቤን ብሰድር ?!
..
ኸሚስ አባ መደድ ፣
ኸሚስ አባ መውደድ ፣
የሓድራ ወናፉን ባድማሱ ሲያጋግም ፣
ምሽቱን ኮልኩሎ እየገሰገሰ ህዋው ሲያስገመግም፣
እየቀጠቀጠ ፣
ደግ እያቀለጠ ፣
ሆሳን ጊዜ ‘ንዲቆርጥ - - የዛገው ቀን ሊሳል ፣
ሞረድ ያዘለው ለይል ...
ሰው በሚል ቡራቁ ከሚኔው ይደርሳል ።
.
የዛኔ ...
ያን የማይሸርፈውን ፣
የመኣና ‘ጀታ አስጨብጠኝ አንተው ፣
ሰው ብዬ ቀን ስዬ ሰው ልሁን እንደሰው ።
..
ምናለ ጌትዬ ...
አንተ ላይሳንህ - - በትናንት መከለስ ፣
በሙሂቦች ቀለም - - በደግ መሰለስ ፣
( አኔም በተመኔ በቀኔ ብቃና ... ! )
በገረረው ንጋት ...
ወዙ በተላሰ ድርቅና ሰንጥቆት በተፍረከረከው ፣
የሙሂቡን ኪታብ ገልጦ ካለመቅራት ...
አይኔን በገለጥከው - - ልሳኔን ባዳንከው !?
ሓድራ መሀል ውዬ - - ሀድራ መሀል ባድር ፣
በቻልኩት ዘምቼ ...
ከዘመኔ አልቦ ላይ የቀልቤን ብሰድር ?!
..
ምናለ ... ?!
_
Semir ami


@semiraklu
3.3K viewsسمير ايمي, 14:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-02 20:48:44
@Abrham_teklu
3.7K viewsAbrsh, 17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ