Get Mystery Box with random crypto!

የልቅ ስለ ወልዲያ ከተማ ላውጋችሁ (ታመነ መንግስቴ ነኝ) በሕይወቴ የወልዲያን ያህል ጓጉቸ ያየ | እዚህ ቤት

የልቅ ስለ ወልዲያ ከተማ ላውጋችሁ

(ታመነ መንግስቴ ነኝ)

በሕይወቴ የወልዲያን ያህል ጓጉቸ ያየሗት ከተማ የለችም

ታሕሳስ 10 ቀን 2014 ዓመተ ምህረት ዕለተ ዕሁድ ረፋድ ወደዚያች ለወራት የተዘጋች ከተማ ስንገባ የተሰማኝን ደስታ ለመረዳት ለቀጣዮቹ አንቀጾች ዕድሜ ተከተሉኝ።

ገባን።ጎንደር በር ጸጥ ብላለች።ነዳን።ፒያሳ ደረስን።"ላል"የሚባል ሆቴል ፊት ለፊት የሰው ፍቅር የጠማቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ተኮልኩለዋል።

የምስል መቅረጫችንን ሲያዩ ይበልጥ ፈነደቁ።ሲበዛ ነፃ ሰዎች ናቸው።መቅረጸ ድምጼን ደቅኘ"እኒያ ቄሱ፣ቄሱ አተረፉን"የሚለውን እስላም ወሎየ ጨምሬ ብሶታቸውን ሰማሁ።

ወዲያውኑ "እኒያ ቄሱ"ወደተባሉት አባት ደብር ነዳን።እሳቸው ኪዳነ ምህረት ቤተ_ክርስቲያን ውስጥ ኖረዋል።በሗላ ስሰማ ብዙዎቹን ያስተማሩባት ደብር ናት።

አጫጭር ግን ወሳኝ ጥያቄዎቸን መለሱ።አቡነ ኤርምያስ ኢትዮጵያ ሰው ፈጥራ የማይደክማት ለም ማኅጸን መሆኗን እንድረዳ የጠቀሙኝ የሕይወቴ ተዓምር ናቸው።

ከዚያም ወዲህ ወልዲያን ተመላልሸባታለሁ።

ሀጂ ያሲን የሚባሉትን የአቡነ ኤርምያስ አቻ አባትም ቃለ_መጠይቅ አድርጌያቸዋለሁ።እሳቸውም የኢትዮጵያ ተስፋ ናቸው።

ወልዲያ የጉባ ላፍቶ ተራራን ተንተርሳ የየጁ መዲና ሆና የቆመች የፍቅር ሐውልት ናት።

በአሁናዊ አቋሟ ከተማ ለማለት ባታመችም ባላት ማኀበራዊ እሴት በቅርብ ዓመታት የሰሜን ኢትዮጵያ ጸሐይ እንደምትሆን ልቤ ይነግረኛል!

እውይ

https://t.me/Gazetaw