Get Mystery Box with random crypto!

' እናቴ_ማርያም_ደጓ_እናቴ' ቀ እንኳን_ለደብረ_ምጥማቅ_አመታዊ_የመገለጥ_በዓል_ በሰላም_በጤና_አ | ፍኖተ ጽድቅ መንፈሳዊ ማህበር አንድ መንበር አንድ ፓትርያርክ አንድ ሲኖዶስ

" እናቴ_ማርያም_ደጓ_እናቴ"

እንኳን_ለደብረ_ምጥማቅ_አመታዊ_የመገለጥ_በዓል_
በሰላም_በጤና_አደረሳችሁ_አደረሰን ◈።
◇ ግንቦት ❷❶_
"እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም"➺በድብረ ምጥማቅ በምትባል ቦታ
ወርቅ ወንበር ላይ ተቀምጣ ለአምስት (5) ቀን የታየችበት ነው።
◇ ጥንት ነገሩ እንዲህ ነው።
ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ስግደት ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ ወደ ምድረ ግብፅና ኢትዮጵያ በተሰደደበት ጊዜ።
◈ ከድንግል እናቱ፣ ከዮሴፍ፣ ከሰሎሜ ጋር በደብረ ምጥማቅ ነበር።
◇ እመቤታችን ቦታውን ስለወደደችው።
ልጇ እንዲህ አላት ይህ ቦታ ወደ ፊት ያንቺ መገለጫ ያሆናል ብሎ ቃል ኪዳን
ገባላት።
እመቤታችን በልጇ ፍቃድ ግንቦት 21 ቀን ከአእላፍ መላእክት፣ ፆድቃን፣
ሰማዕታት አስከትላ መታ ለአምስት ቀን ና ለክርስቲያኑና ለአሕዛቡ የተገለፀችበት
ቀን ነው።
◈➺ ይህም በዓል ከ33ቱ የእመቤታችን በዓላት አንዱ ሲሆን በዚህ ቀን ግብጽ
ደብረ ምጥማቅ በተባለ ቦታ በተሰራች ቤተክርስቲያን እመቤታችን ጻድቃንን
መልአክትን አስከትላ ትገለጽላቸው ነበር።
እስላምም ክርስቲያንም በግልጽ ይመለከቷት ነበር።
◈ ከየአገሩ ያሉ ሰዎች ይሰበሰባሉ ድንኳን ተክለው ሰቀላ ሰርተው አጎበር ጥለው
ይከትማሉ ፤ ድንግልም ከግንቦት 21 ቀን ጀምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት
ሳታቋርጥ ትገለጽላቸው ነበር፤
◇ ህዝቡ የተለያየ ጥያቄ ይጠይቃታል አዳም አባታችንን አሳይን? ይሏታል
◈ ገሚሱ ነብዩ ዳዊትን
◈ ገሚሱ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሳይን ይሏታል?
◈ አንዳንዱም ከዚህ ቀደም የሞተ ዘመዱን እንድታሳየው ይጠይቃታል?
◇ እርሷም ለሁሉም ፍቃዳቸውን ትፈጽምላቸው ነበር፤
አዳምን ስትጠራው ከሔዋን ጋር
ዳዊትን ስትጠራው ከበገናው ጋር ቅዱስ ጊዮርጊስን ስትጠራው ከጸአዳ ፈረሱ
ጋር ነው።
◇ ወይ ግሩም ታዲያ ይህ በዚያ ደጉ ዘመን ነበር፤
◇ አሁን ግን ኃጢያታችን ሲበዛ በረድኤት ወይም ለበቁ ካልሆነ
በገሃድስ ተገልጻ አትታይም።
➺ ለእናቱ ለቅዱስተ ቅዱሳን ለንፅህተ ንፁሀን
◈ ለአዛኝቷ ድንግል እመቤቴ ለቅድሳን እናታቸው
◈ ለነቢያት ትንቢታቸው
◈ ለሰማእታት እክሊላቸው ለሆነች ለእናቱሲል ይማረን። ኣሜን፫
➺◇በቃቹህ ይበለን ከመጣብን ከዚህ ክፉ የዘር በሽታ በቃችሁ ይበለን።
የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ፍቅሯ በልባችን ጣዕሟ በአንደበታችን
ይደርብን።
➺ወስብሐት ለእግዚአብሔር
➺ወለወላዲቱ ድንግል
➺ወለመስቀሉ ክብር


https://t.me/fenot2