Get Mystery Box with random crypto!

ክፍል (45) #ነገረ ድኅነት #በነገረ ድኅነት የምስጢረ ተዋህዶ #ምሳሌዎች ሀ /የእሳትና #ብረት | ሐረር ፈለገ ሕይወት ሰ/ት/ቤት

ክፍል (45)
#ነገረ ድኅነት
#በነገረ ድኅነት የምስጢረ ተዋህዶ #ምሳሌዎች
ሀ /የእሳትና #ብረት ውህደት
(የጋለ ብረት)
#ብረትና እሳት #ሲዋሐዱ ብረቱ ከእሳት በገባ ጊዜ #እሳቱ #የብረቱን ገነዘብ
(ባሕርይ ) ገንዘብ ያደርጋል #ብረቱም የእሳቱን ገንዘብ ያደርጋል ልክ መለኮት የሥጋን ሥጋም የመለኮትን#ገንዘብ ገንዘብ እንዳደረጉት ማለት ነው።
የቃል (መለኮት ) ገንዘብ #የሥጋ ሆነ ።
#የሥጋ ገንዘብም ከኃጢአት በስተቀር የቃል ሆነ
" ሃይ አበው ዘቄርሎስ
#እሳት ረቂቅና ብሩህ ነው ነገር ግን #የብረትን ገንዘብ ገንዘብ በማድረግ በተዋሐዱ ጊዜ
ግዙፍ(የሚያዝ የሚጨበጥ የሚዳሰስ ) ነው።
#እንደዚሁም #ሥጋ በባሕርይው ግዙፍና ውሱን ነው
#መለኮትን በተዋሐደ ጊዜ ግን
#በመለኮት ገንዘብ ረቂቅ ምሉዕ ክቡር ባለጸጋ ነው ።
#መለኮትም በሥጋ ገንዘብ (ሥጋን በተዋሐደ ጊዜ ) ግዙፍና ውሱን ነው።
#ዳግመኛም የእሳትና የብረት ተዋህዶ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ
#የሕማሙ (የተቀበለው መከራ) አምሳል ነው።
#እንደ እሳቱ የማይዳሰሰው የማይያዘውና የማይጨበጠው #ረቂቁ መለኮት እንደብረቱ የሚዳሰሰውን የሚያዘውና የሚጨበጠውን ሥጋን በመዋሐዱ ነው ።
#እንግዲህ አምላክ ተያዘ ታሰረ ተገረፈ ተሰቀለ ሞተ ተቀበረ ተነሳ አረገ #የምንለው በሥጋ ሞተ #በመንፈስ ግን ሕያው ሆነ
( 1ኛ ጴጥ 3 ÷ 18 )
ስብሐት ለሥላሴ
ይቀጥላል
ቀሲስ ጥሩውኃ ክፍሌ።