Get Mystery Box with random crypto!

Ministry of Labor and Skills - Ethiopia

የቴሌግራም ቻናል አርማ fdre_mols — Ministry of Labor and Skills - Ethiopia M
የቴሌግራም ቻናል አርማ fdre_mols — Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
የሰርጥ አድራሻ: @fdre_mols
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 12.48K
የሰርጥ መግለጫ

FDRE, Ministry of Labor and Skills

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-12-03 11:13:36
2.2K views08:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-03 11:13:33 የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር " ሚሊዮን ፈተናዎች፤ ሚሊዮን ዕድሎች" በሚል መሪቃል እያካሄደ የሚገኘው የኢንተርፕሪነርሺፕ ሳምንት ዛሬም ቀጥሏል።

ፐብሊክ ኢንተርፕሪነርሺፕ ቀዳሚው ውይይት እየተካሄደበት የሚገኝ ርዕሰ ጉዳይ ሲሆን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ስምሪት እና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ንጉሡ ጥላሁን እንደተናገሩት ያሉትን መልካም አሰራሮች ለማጎልበት እና እንቅፋት የሆኑትን ለመለወጥ ስለ ፐብሊክ አንተርፕርነርሺፕ መወያየት ጠቃሚ ነው ብለዋል።

ከውይይቱ የፐብሊክ አንተርፕርነርሺፕ ምንነትን በበቂ ደረጃ በማብራራት ለአሰራር ጠቃሚ የሆነ ውይይት ማድረግ እንደሚጠበቅ ገልፀዋል።

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አመራር እና ሰራተኞች ቀደም ሲል የፐብሊክ ኢንተርፕሪነርሺፕ ስልጠና የወሰዱ ሲሆን የተለያዩ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችም ስልጠናውን መቀጠላቸው ተገልጿል።
2.1K views08:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-02 11:10:08
2.2K views08:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-02 11:10:03 “ችግር የማያቆመው ትውልድ በመፍጠር ሂደት ውስጥ ኢንተርፕሪነርሺፕ ልዩ ሚና አለው”
ክቡር ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር)
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ

ዓለም አቀፍ የኢንተርፕሪነርሺፕ ሳምንት አስመልክቶ የኢንተርፕሪነርሺፕ አተገባበርና ሚና በቴክኒከና ሙያ እና በትምህርትና ስልጠና ተቋማት በሚል ርዕስ የተዘጋጀዉ የፓናል ዉይይት በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

‹‹ኢንተርፕሪነሮች ችግርን ወደ ዕድል የሚቀይሩ ናቸው ስንል ችግር የማያቆመው ትውልድ በመፍጠር ሂደት ውስጥ ኢንተርፕርነርሺፕ ልዩ ሚና እንዳለው በመተማመን ነው›› ያሉት በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ናቸው፡፡

የሥራና ስልጠና ሂደትን በኢንተርፕርነርሺፕ እሳቤ ለመቃኘት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተለያዩ ስልጠናዎችን ሲሰጥ መቆየቱን በማስታወሰ ኢንተርፕርነርሺፕ በማሰልጠኛ ተቋማት ውስጥ እንደ አንድ ኮርስ ከመስጠት ባለፈ ባህል እንዲሆን ሰፊ ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑን ያነሱት ክቡር ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ተቋማቱ ከመንግስት ጥገኝነት ተላቀው ማህበረሰቡ ላይ ተፅዕኖ ፈጥረው እንዲያገለግሉ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ሳምንቱን ምክንያት በማድረግ የተሰናዳው የውይይት መድረክም የፈጠራ ሥራዎችን ማበልፀጊያ ማዕከላት ከገበያ ጋር ትስስር የሚፈጥሩበትን፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በማስቀረት እና ወደ ውጭ ጥራት ያላቸውን ምርቶች አምርቶ ለመላክ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ረገድ ውጤታማ እንዲሆኑ ለሚደረገው ጥረት አመላካች እና ለተግባራዊነት የሚመቹ ሃሳቦች የሚቀርቡበት ይሆናል ብለዋል፡፡

በውይይት መድረኩ ላይ የኢንተርፕሪነርሺፕ ትምህርት አቀራረብ እና የተለያዩ የትምህርት ተቋማት ተሞክሮ ፣ ሥራ ፈጣሪነት በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ያለው ሚና እና አስፈላጊነት እንዲሁም አንድ ተቋም የኢነተርፕሪነሪያል ለመባል ሊያሟላ የሚገባውን የትምህርት ይዘት በተመለክተ መነሻ ሃሳቦች ቀርበው ውይይት ተካሂዷል፡፡

“ ሚሊዮን ፈተናዎች ሚሊዮን ዕድሎች” በሚል መሪ ቃል የተለያዩ ሁነቶች የሚስተናገዱበት ሀገር አቀፍ የኢንተርፕሪነርሺፕ ሳምንት አራት ዋና ዋና የትኩረት ሃሳቦች ያሉት ሲሆን የኢንተርፕርነርሺፕ ስነ_ ምህዳር፣ ትምህርት፣ አካታችነት እና ፖሊሲ ላይ በማትኮር እየተከናወነ ይገኛል፡፡
2.2K views08:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-01 18:30:37
3.2K views15:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-30 14:34:23 ተግዳሮቶች ጠንክረን ከሰራንባቸዉ እድሎች ናቸዉ"፡፡

ክብርት ሙፈሪሃት ካሚል
የሥራና ክህሎት ሚንስትር

ዓለም አቀፍ የኢንርፕሪነርሺፕ ሳምንት ፕሮግራም ሚሊዮን ፈተናዎች፤ ሚሊዮን እድሎች በሚል መሪ ቃል በይፋ ተጀመረ፡፡

በፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት በተጀመረዉ እና በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የተሰሩ የተለያዩ የፈጠራ ዉጤቶች ለጉብኝትና ልምድ ልዉዉጥ በቀረቡበት በዚህ መድረክ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችን ጨምሮ በርካታ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡

በመድረኩ መዕክት ያስተላለፉት የሥራና ክህሎት ሚንስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ተግዳሮቶችና ችግሮች ጠንክረን ከሰራንባቸዉ እድሎች ናቸዉ ሲሉ ገልጸዋል፡፡

የአለም አቀፍ የኢንተርፕረነርሺፕ ሳምንት በአንድ ሳምንት ተከብሮ የሚያልቅ አለመሆኑ ጠቁመዉ ይልቁንም አመቱ ሙሉ ለምንሰራቸዉ ስራዎች ሃሳብ የምንለዋወጥበት እና ባለድርሻ አካላትን የምናገኝበት መድረክ ነዉ ብለዋል፡፡

የኢንተርፕሪነር አስተሳሰብ ባህል አድርጎ ለመገንባት ሰፋፊ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የገለጹት ሚንስትሯ እንደ ሀገር ለተጀመረዉ ለዉጥ እንዲሁም ለቴክኖሎጂ ሽግግር ትልቅ አስተዋጽዎ እንደሚኖረዉም አብራርተዋል፡፡

የቴክኒክና ሙያ ተቋማት በየጊዜ የሚያፈልቋቸዉ ሀሳቦች ሼልፍ ላይ የሚቀመጡ ሳይ ወደ ተግባር ተቀይረዉ ችግር የሚፈቱ፣ ስራ እና ሀብት የሚፈጥሩ ለማድረግ ከሚመለከታቸዉ ሚኒስትር መስሪያ ቤቶች በጋራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ንጉሱ ጥላሁን በበኩላቸዉ በዚህ የኢንርፐሪነርሺፕ ሳምንት የቴክኖሎጂ ዉድድር፣ የጀማሪ ኢንርፕራይዞች ዉድድር፣ ኤግዚቢሽንና ልምድ ልዉዉጥ ፣ የቴክኒክና ሙያ እና ዩኒቨርስቲዎች የትምህርት አሰጣጥ እና ኢንተርፕረነረሺፕ እና የፐብሊክ አንተርፐሪነርሺ ላይ የሚመክር አወደ ጥናት እና ሌሎችም በርካታ ስራዎች ማስጀመሪያ ፕሮግራም ነዉ ብለዋል፡፡

በዕለቱ የተለያዩ የፈጠራ ስራ ዉጤቶች ተጎብኝተዋል፡፡
3.8K views11:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ