ሰበር ዜና
በትናንትናው ዕለት ከገረሴ ዙርያ ወረዳ 12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ለመፈተን አርባምንጭ ጫጮ ካምፓስ የመጣች ተማሪ በሰላም ተገላገለች::
ተማሪ መድኃኒት መርጊያ የገረሴ ዙርያ ወረዳ የደንብሌ ኦቶራ 2ኛ ደረጃ የማህበራዊ ሳይንስ የማታ ተማሪ የነበረች የሰባት ወር ዕርጉዝ ስትሆን በሰላም መንትያ ልጆችን ተገላግላለች፡፡
በአሁኑ ሰዓት ህፃናት በማሞቂያ ክፍል በጥሩ ጤንነት ላይ ይገኛሉ፡፡