ዛሬ ፒያሳ በዕድሳት ላይ የነበረ ቤት ተደርምሶ በሰዉ ላይ ጉዳት ደረሰ
ዛሬ ግንቦት 13 ቀን 2015 ዓ.ም ረፋድ 4 ሰዓት በእድሳት ላይ የነበረ ቤት ተደርምሶ በሰዉ ላይ ጉዳት ደርሷል። በአራዳ ክፍለ-ከተማ ወረዳ 10 ፒያሳ ደሀብ ሆቴል አጠገብ በእድሳት ላይ የነበረዉ አንድ ካፌ ተደርምሶ በዚያዉ ስፍራ በመንገድ ላይ ሻይ ከሚሸጡት መካከል 5 ሰዎች ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሷባቸዋል።
ጉዳት ከደረሰባቸዉ ተጎጂዎች ዉስጥ ሶስቱ በእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አንቡላንስ ወደ ጤና ጣቢያ ተወስደዋል ። የእድሳትና የግንባታ ስራዎች በሚከናወኑበት ጊዜ መሰል አደጋዎችን ለመከላከል አስፈላጊዉን የደህንነት መስፈርቶችን አሟልቶና ጠብቆ መስራት አስፈላጊና ግዴታም ጭምር ያለበት በመሆኑ ልዩ ትኩረትም እንዲሰጠዉ ኮሚሽን መ/ቤቱ አሳስቧል።
@fastmereja