የ186ቱ ታማሚዎች ዝርዝር ሁኔታ
በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገ 4034 የላቦራቶሪ ምርመራ 186ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 5,034 ደርሷል።
የታማሚዎችን ሁኔታ ስንመለከት
-181 ኢትዮጵያውያን እና 5 የውጪ ዜጎች ሲሆኑ 73ወንድ እና 113ሴት ናቸው። እድሜያቸው ከ6ወር-75 አመት መሆናቸው ተገልጿል።
የመኖሪያ ቦታቸውን ስንመለከት
_
•147ሰዎች- ከአዲስ አበባ
•16ሰዎች- ከሱማሌ ክልል
•4ሰዎች -ከኦሮሚያ ክልል
•10ሰው - ከአፋር ክልል
•8ሰዎች- ከድሬዳዋ
•1ሰው- ከደቡብ ክልል
በሌላ መልኩ በትላንትናው ዕለት ሰባ አራት (74) ሰዎች (63 ከአዲስ አበባ፣ 6 ከትግራይ ክልል፣ 2 ከሶማሊ ክልል፣ 2 ከደ/ብ/ብ/ሕ ክልል፣ እና 1 ሐረሪ ክልል) ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 1486 ነው።