Get Mystery Box with random crypto!

ETHIO ZENA (ኢትዮ ዜና)🇪🇹🇪🇹🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiozena24 — ETHIO ZENA (ኢትዮ ዜና)🇪🇹🇪🇹🇪🇹 E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiozena24 — ETHIO ZENA (ኢትዮ ዜና)🇪🇹🇪🇹🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @ethiozena24
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.26K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል የሀገር ውሥጥ እና የውጭ ሀገር ዜናዎችን በፍጥነት ይደርስዎታል

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-07-11 18:35:22 #አስቸኳይ_ሰሜን_ሸዋ!!

ለጊዜው ሰልጣኞቹ እነማን እንደሆኑ ባላረጋግጥም የተሀድሶ ፕሮግራም በሚል ስልጠና ላይ ሰንብተው በትናንትናው እለት ጧት ግብዣ ነበራቸው፡፡ ጥቃቱን የጀመሩትም ትናንትና ነው፡፡

የተነሱት ከበጤ ሲሆን አሁን ባለፈው ያወደሟትን ሞላሌ አልፈው አርሶ አምባ ላይ ቤቶች እያቃጠሉ ነው፡፡ ወራሪዎቹ ወደ5 የሚሆን ዲሽቃ ያላቸው በመሆኑ ቤቶችን በርቀት እያወደሙ ይገኛሉ፡፡ ለሸዋሮቢት አቅራቢያ ወደሆነችው ኩሪብሪ እየተጠጉ ሲሆን የኩሪብሪ ነዋሪ ወደሸዋሮቢት ተሠዷል፡፡

በአካባቢው የነበረው የተወሠነ ልዩ ሀይል ወራሪዎቹን ለማስቆም ጥቂት ሙከራ ያደረገ ቢሆንም ፥ አሸባሪዎቹ በከባድ መሳሪያ የታገዙና የተደራጁ በመሆናቸው በአሁኑ ሠአት ትቷቸዋል፡፡ ከሰሞኑ መንግስታዊ ዘመቻ ጋር ተያይዞም በስፍራው አንድም የፋኖ ሀይል ባለመኖሩ ለልዩ ሀይሉ እገዛ ሊያደርግ አልተቻለውም፡፡

ይህ "ኦነግ-ሸኔ" ብዬ በዳቦ ስሙ ለመጥራት የተገደድኩት ቡድን ፥ በአስቸኳይ ካልተገታ ሸዋሮቢት ከተማን ጭምር ለውድመትና ጉዳት እንዳይዳርጋት እሰጋለሁ፡፡
በተጨማሪም በስልክ ያነጋገርኩት ጓደኛየ እንደሚለው አሁን ተኩሱ እየተባባሰ መምጣቱን ይናገራል አክሎም ዝግጅቱን ቀድመው የኛዎቹ ብአድኖች ማለትም የአማራ ብልፅግና ይሁንታን ያገኘ ይመስለኛል ብሏል ።ለምን እንድህ አልክ ብየ ለጠየኩት ጥያቄ ዋና ዋናዎቹን የፋኖ አዛዦችን ለስብሰባ ብለው አታለው አስረዋቼዋል እናም አሁን ያለማንም ከልካይ ቤቶችን እያወደሙ ነው ።
#ሼር ያድርጉት!

መረጃው የዘሪሁን ገሰሰ ነው!

https://t.me/ETHIOZENA24
1.5K views🅝🅔🅖🅡🅞 🅜🅐🅝, edited  15:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 17:11:40
ኦነግ/ሸኔ በአጣዬ ከፍተኛ ተኩስ መክፈቱ ተነገረ!

ኦነግ/ሸኔ፣በሰሜን ሸዋ፣ አጣዬ ከተማ፣ ልዩ ቦታዋ በጤ በምትባል አካባቢ፣ ዛሬ ጠዋት ጀምሮ ከፍተኛ የተኩስ ድብደባ እያደረገ መሆኑን ተሰምቷል።

በአሁኑ ሰዓት በጤ በምትባለው አካባቢ የአማራ ልዩ ኃይል ከኦነግ/ሸኒ ጋር የተኩስ ልወውጥ እያደረገ ይገኛል። በተኩስ ልውውጡም ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች መቁሰላቸውን ምንጮች ከቦታው መረጃ አረጋግጠዋል።

በኦሮሞ ሊህቃንና ጃዋር መሀመድ በሚያስተዳድረው ሚዲያ በኩል በሚቀሰቀሱ ጦርነቶች ምክንያት በአሁኑ ሰዓት ኦነግ/ሸኔ ከፍተኛ የሆነ ኃይል በመያዝ ወደ አጣዬ እያመራ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
1.4K views🅝🅔🅖🅡🅞 🅜🅐🅝, edited  14:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 17:10:55
በተለያዩ ክልሎች የአማራ ብሔር ተወላጆች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን መንግሥት ማስቆም አልቻለም ያሉ 10 ሲቪክ ማሕበራት ዓለም አቀፍ ተቋማት እንዲያስቆሙ ጠየቁ።

ማሕበራቱ በደብዳቤው ባለፉት 4 ዓመታት ጥቃቶቹ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና በኦሮሚያ ክልሎች መፈጸማቸውን አመልክተዋል። በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢ ወረዳ ቶሌ ቀበሌ ሰኔ 11፤2014፤ 338 ሰዎች መገደላቸውን መንግሥት አስታወቋል። የአማራ ማህበር በአሜሪካ በበኩሉ ከ500 በላይ ሰዎች እንደተገደሉ ማረጋገጡን ገልጿል።

ከቀናት በኋላም በቄለም ወለጋ መንገድ ሃያና ሮቢት ገበያ በተባሉ መንደሮች «ኦነግ ሸኔ» በተባለው ቡድን ታጣቂዎች ግድያ መፈጸሙን በርካቶች መፈናቀላቸውን፤ 50 የሚሆኑ ደግሞ ታፍነው መወሳደቸውን ደብዳቤው ዘርዝሯል። ደብዳቤው «የአማራ ተወላጆች ጅምላ ግድያ» ያለው ተግባር በጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ አስተዳደርም ሆነ በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትኩረት ተነፍጎታል ሲል ይወቅሳል። የሸዋ ልማትና ሰላም ማሕበር በጎ ፈቃደኛ ሥራ አስኪያጅ ረዳት ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቸው፤ «የአማራ ክልል መንግሥት ከክልሉ ውጪ ያሉ አማሮችን ደህንነትና ሰላም ለማስጠበቅ ጠንካራ አቋምና ተቆርቋሪነት አያሳይም» ብለዋል።

የተባበሩት አማራ የበጎ አድራጎትና ልማት ማሕበር ፕሬዝደንት ረዳት ፕሮፌሰር ማዕረጉ ቢያበይን በበኩላቸው ደብዳቤው የተላከው «ችግሮች ከዛሬ ነገ ይሻሻላሉ የሚል እሳቤ ቢኖርም እየባሰ በመሄዱ» እንደሆነ ገልጸዋል። የተጻፈውም፣ ለተመድ የፀጥታው ም/ቤት፣ ለተመ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን፣ ለተመድ ሰብአዊ መብት ጉባኤ፣ ለተመድ ሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት፣ ለአፍሪካ እና ለአውሮጳ ሕብረት፣ ለአምነስቲ ኢንተረናሽናል፣ ለሂውማን ራይትስ ዎችና ለዓለም አቀፍ ዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ መሆኑን ተገልጿል።
1.4K views🅝🅔🅖🅡🅞 🅜🅐🅝, 14:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 23:18:18
"…ያለፈውን ፩ወር ሙሉ ህዝቡ የሃገሩን መንግሥት መላ ዘይድልን ወይም ለሚችል ሌላ አካል ቦታውን ልቀቅ ብሎ በሰላማዊ ሰልፍ ሲያሳስበው ሰነበተ። መንግሥቱ ግን " ቢሮ ቀለም እየቀባ፣ መናፈሻ እየገነባ፣ ለራሱ ዘጭ ያለ ኑሮ እየኖረ ህዝቡን ጥፋ ከዚህ ብሎ ገገመ። ታዲያ ዛሬ ህዝቡ ወደ ቤተ መንግሥት ተመመ። በዚያም መጀመሪያ ላይ የጠበቃቸው ከባድ ነገር ነበር።

"…እስከ አፍንጫው የታጠቀ የሃገሪቱ ሁሉም አይነት ሰራዊት ነበር የጠበቀው። ልክ እንደኛው (መከላከያ፣ ፌደራል ፖሊስ፣ ሪፐብሊካን ጋርድ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ የኦሮሚያ ፖሊስ፣ የኦሮሚያ ልዩ ኃይል፣ ሚኒሻ ከቡራዩና ከሰበታ ከሱሉልታም መንግሥታችን ተነካ ብለው የመጡት ሳይቆጠሩ ማለት ነው።) ብቻ ከሃገሪቱ የጸጥታ ኃይል የቀረ አልነበረም።

"…የጭስ ቦንብ ተኮሱበት፣ የእሳት አደጋ ውኃ ማጥፊያ አምጥተው ህዝቡ ላይ ረጩት። ገፈተሩት፣ ቀጠቀጡት። ህዝቡ ግን የተራበ ስለነበር ንቅንቅ አላለም። ወይ ፍንክች። የቡድሀ የሃይማኖት አባቶችም ከፊት ተሰለፉ። ፖሊስም ደከመው። ሁኔታውን ሲያይ ህዝቡ በቀላሉ የሚፋታው አለመሆኑም ገባው። ስንቱንስ ገድሎ ይዘልቀዋል። አፈገፈገ። ህዝቡም ጥሶ ቤተ መንግሥት ገባ።

"…እና ምን ለማለት ነው። ለውጡ እንዲሁ አልመጣም። ፕሬዘዳንቱም እኔ ከወረድኩ 100 ሺ ሰው ይታረዳል አላሉም። ቢሉስ የራበው ሰው መታረዱ ቢቀርለት ረሃብ ይፈጀው የለም? እናም ህዝቡ በራብ ከመሞት በሰይፍ መሞትን መረጠ። ሳንቲም ኖሮህ ቤትህ ምግብ እንዳለ እያወቅህ ሲርብህ እኮ እንዴት እንደሚያደርግህ ይታወቃል። ወዳጄ ራብ ከባድ ነው።

"…120 ሚልየን ህዝብ ያላት ሃገር በአንድ ወፈፌ አውቆ አበድ ትከሻ ላይ ዘፍዝፎ ዝም ብሎ መተኛት ነውር ነው። የሆነሆኖ የራበው ህዝብ በቆስጣ ብቻ አይኖርም። መሪዎቹን ሳይበላም አይመለስም።

"…ሁልጊዜ ህዝብ ያሸንፋል…!
1.5K views🅝🅔🅖🅡🅞 🅜🅐🅝, 20:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 13:17:10 Channel photo updated
10:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 13:13:55 አብይ አህመድ ማለትኮ!!!

➔ኦነግን ከእነ ትጥቁ አስገብቶ ተጨማሪ ወጣቶችን የሪፑብሊክ ጋርድ ጠመንጃ ያስታጠቀ፤

➔ያደራጀውን የሽብር ድርጅት ሥም "ሸኔ" በሚል ባለቤት አልባ ሥም የደበቀ፤

➔የሮዋንዳን የጭፍጨፋ ታሪክ በኢትዮጵያ ምድር ለመድገም የሚያስችል ሞት የማለማመድ ተግባር ውስጥ የተዘፈቀ፤

➔የአማራዎችን ሕይወት ከአትክልት በታች ያወረደ፤

➔አገር የማፍረስ ተልዕኮ ይዞ ወደ ሥልጣን የመጣ፤

➔በአማራ ላይ የጥላቻ ስብከትን በግልጽ የሚያስተላልፉ ኃይሎችን ከመፍጠር አልፎ፣ እራሱም የጥላቻ መምህር ሆኖ ባስተላለፈው ስብከት አማራዎችን ለእልቂት የዳረገ፤

➔አገሪቷን ቀርቶ አንደበቱን መቆጣጠር የማይችል፤

➔ስንቱን የአማራ ክልል አመራር አሽቀንጥሮ ሲጥል የሽመልስ አብዲሳን ካቢኔ የማይሻር አድባር ያደረገ፤

➔ብአዴን የተባለውን ድርጅት በሆዳሞች ሞልቶ ያለ ጠባቂ የሚጨፈጨፍ ሕዝብ የፈጠረ፤

➔ስልጣኑን መልቀቅ ብቻ ሳይሆን በዘር ማጥፋት ወንጀል መጠየቅ የሚገባው፤

https://t.me/ETHIOZENA24
1.3K views🅝🅔🅖🅡🅞 🅜🅐🅝, edited  10:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 19:58:08 በነገራችን ላይ ለዐማራ ህዝብ ጭፍጨፋ ትልቁ ምክንያት ነሐሴ 15 ቀን 1987 ተደንግጎ የወጣው የህወሓት እና የኦነግ "የተሰነይ ማኒፌስቶ" በመባል የሚታወቀው ሕገመንግሥት ተብዬው ነው።

ልብ ብላችሁ ተከታተሉኝማ፣

ሕወሓት እና ኦነግ ተጨቆኑ የሚሏቸውን ብሔሮች "ነጻ የሚያወጣ" ሰፋ ያለ መብት የሚሰጥ ሕገመንግሥት ሲያወጡ፣ ጨቋኝ ነበር የተባለውን የዐማራ ሕዝብ በስብሰባው ላይ ተወካይ እንኳን እንዳይኖረው አድርገዋል። በሰኔው 83'ቱ የሽግግር ወቅት ጉባኤም ሆነ በኋላም በ1987 ሕገ መንግሥት በማርቀቁ ሂደት ዐማራው በብሔር ደረጃ አልተወከለም።

በጣም የሚያስገርመው በወቅቱ ከ80 ሺህ ሕዝብ የማይበልጥ ሕዝብ ያለው "የም" ሲወከል፤ በ1999 ዓ.ም. ሕዝብና ቤት ቆጠራ እንኳን የሕዝብ ቁጥሩ ከ180 ሺህ የማይበልጠው ሐረሬ ወይም አደሬ በንቅናቄ ፓርቲ ሲወከል፤ ከሀገሪቱ 1/3ኛ በላይ የሚሸፍነው ዐማራ የሚባል ነገድ ሳይወከል ቀረ።

ለዐማራ ህዝብ ሞት፣ መፈናቀልና ስደት ምክንያት የሆነው የወያኔና የኦነግ ሕገመንግሥት ተመርኩዞ የተነደፈው የክልሎች ሕገመንግሥትም በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ዐማሮችም እውቅና አይሰጥም።

በአንጻሩ፤ የዐማራ ህዝብ 81.5 በመቶ አካባቢ በሚሸፍነው ክልል ውስጥ የዋግኸምራ፣ የአዊ፣ የአርጎባ፣ የኦሮሞና የቅማንት ብሔረሰቦች ማንነታዊ አስተዳደር ተሰጥቷል።

ለምሳሌ፤ በኦሮሚያ ክልል የሚኖረው የዐማራ ነገድ ከ20 ሚሊዮን በላይ ይሆናል ተብሎ ይገመታል። ይህም በክልሉ ከሚኖሩት ነገዶች መካከል ከኦሮሞው ቀጥሎ በሕዝብ ብዛት በሁለተኛ ደረጃ እንደሆነ የህዝብ ቤት ቆጠራ ያሳያል። በኦሮሚያ ክልል የዐማራ ህዝብ በሁለተኛ ደረጃ የሚገኝ ቢሆንም የዐማራ ብሔረሰብ ልዩ ዞን የለም።
የኦሮሚያ ሕገመንግሥት ምዕራፍ 2. አንቀጽ 8. እንዲህ ይላል፣ "የኦሮሞ ህዝብ የክልሉ የበላይ ሥልጣን ባለቤት ሲሆን፣ የህዝቡ የበላይነትም የሚገለጸው በሚመርጣቸው ተወካዮችና ራሱ በቀጥታ በሚያደርገው ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ ነው"

በአንጻሩ በአማራ ክልል ውስጥ የኦሮሞ ብሔረሰብ ድርሻ ከክልሉ ሕዝብ 2 ከመቶ ብቻ ቢሆንም፤ "የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን" የሚል አጥር ግን ተፈጥሯል።

በኦሮምያና በሌሎችም ክልሎች የሚኖረው በሚሊዮን የሚቆጠረው ዐማራ ግን ማንነቱ ተክዶ፣ እንደሌለ ተቆጥሮ ምንም የፖለቲካ መብት እንዳይኖረው ተደርጎ በሁለተኛ ደረጃ የክልል ነዋሪነት የጨለመ ሕይወቱን በመግፋት ላይ ይገኛል። የብሄር ማንነትን መሠረት ያደረገ ፌደራላዊ አወቃቀር በምትከተል ሀገር የኦሮሚያ፣ የደቡብ፣ የቤንሻንጉልና ሌሎችም ክልሎች የፌደራሉ ሕገ መንግስት ካስቀመጠው መርሆ በተቃራኒ በእነዚህና በሌሎች ክልሎች የሚኖሩ ዐማሮች በቂ ሕጋዊ፣ አስታደራዊና ፖለቲካዊ መብት አለመሰጠቱ የሚያስገርም ነው።

በ1999 ዓ.ም. የሕዝብና የቤት ቆጠራ መሠረት በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባጠቃላይ የነዋሪው ብዛት 748,345 ነው። ከዚህ ቁጥር ውስጥ በርታ 199,303 ሲሆን፣ በሁለተኛ ደረጃ ዐማራው 170 ሺህ ነው። ነገርግን የክልሉ ሕገመንግሥት ባለቤት የሚላቸው በርታን፣ ከዐማራ ያነሰ ቁጥር ያላቸውን ቁጥራቸው 160 ሺህ የሆኑትን ጉሙዝን፣ ቁጥራቸው 60 ሺህ የሆኑትን ሽናሻንና 15 ሺህ የሚሆኑትን ማኦን ብቻ ነው። የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሕገመንግሥት አንቀጽ 2. እንዲህ ይላል፣ "በክልሉ ውስጥ የሚኖሩ ሌሎች ሕዝቦች የሚታወቁ ቢሆንም የክልሉ ባለቤት ብሄር፣ ብሄረሰቦች በርታ፣ ጉሙዝ፣ ሽናሻ፣ ማኦና ኮም ናቸው" ይላል። በክልሉ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ዐማራ እንኳን መሥራች ሊባል ቀርቶ ማንነቱ እንኳን ተሰርዟል።

በ1999 የሕዝብና የቤት ቆጠራ መሠረት በጋምቤላ ክልል የሚኖረው የዐማራ ህዝብ 25,862 ነው። ማኦ 64 ብቻ ናቸው። ማኦ የተሰኘው ብሔረሰብ ከዐማራው ቁጥር እጅግ አነስተኛ ቢሆንም በጋምቤላ "መሥራች ብሔረሰብ" ተብለዋል።

ባጠቃላይ በስምንቱም ክልሎች በብዙ ሚሊዮን የሚቈጠር የዐማራ ህዝብ መኖሩ እየታወቀ በያለበት ራስ ገዝ እንዲሆን፣ መንግሥታዊ ውክልና እንዲኖረው፣ በቋንቋውና በባህሉ እንዲጠቀም አልተፈቀደለትም። አሁን አለ የሚባለው ፌደራሊዝም በሚደነግገው መሠረት በኦሮምያ ሆነ በሌሎች ክልሎች የሚኖሩ ዐማሮች ባሉበት አካባቢ የራሳቸውን ዕድል በራሱ እንዳይወስኑ፣ ማንነታቸው ተጠብቆ፣ ባህላቸውንና ቋንቋቸውን እንዳያሳድጉ፣ በቋንቋቸው እንዳይዳኙ ተጨፍልቀው ይገኛሉ። እንዲህ ዜግነታዊ መብቱን ገፈው፤ የመምረጥና የመመረጥ መብት ነፍገው ሲያበቃ የተከተሉት ዘዴ ዐማራ "መጤ" ነው የሚል ወካይ ስም በመስጠት መግደል ነበር።

ለዚህም ነው የኢትዮጵያ ሕገመንግሥት ተብዬው ተቀዶ ቆሻሻ ገንዳ ውስጥ መጣል አለበት የምለው። ይህ ሕገአራዊት እንዲቀየር ከፍተኛ ትግል ከሁላችንም የሚጠበቅ ይሆናል። ለዐማራ ህዝብ ስቃይ ምንጩ ይህ የተሰነይ ማኒፌስቶ ነው።

https://t.me/ETHIOZENA24
1.4K views🅝🅔🅖🅡🅞 🅜🅐🅝, edited  16:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ