የትግራይ መምህራን ማኅበር የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የመምህራንን የ2015 ዓ.ም የአምስት ወራት ውዝፍ ደመወዝ እንዲከፍል ጥሪ አቀረበ፡፡ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ውዝፍ ክፍያውን ለመክፈል ቀደም ሲል ተስማምቶ እንደነበር የማኅበሩ ም/ፕሬዝዳንት ንግስቲ ጋረደ ለክልሉ ቴሌቪዥን ተናግረዋል። ይሁን እንጂ አስተዳደሩ ለመክፈል ቃል የገባውን የአምስት ወራት ደመወዝ አለመክፈሉን ም/ፕሬዝዳንቷ ገልፀዋል። በክልሉ የሚገኙ መምህራንን የ17 ወራት ደመወዝ አልተከፈለንም ሲሉ ሰልፍ መውጣታቸው ይታወሳል። ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች ቻናል https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0 Share share ለተጨማሪ መረጃ ╔═══════════╗ @ethiouniversity1 @ethiouniversity1 @ethiouniversity1 ╚═══════════╝ 16.7K views11:21