Get Mystery Box with random crypto!

#መቐለ ዛሬ በመቐለ #ሰላማዊ_ሰልፍ የወጡ የመቐለ ዩኒቨርሰቲ ተማሪዎች በፖሊስ ድብደባና እስራት | 🇪🇹ኢትዮ University

#መቐለ

ዛሬ በመቐለ #ሰላማዊ_ሰልፍ የወጡ የመቐለ ዩኒቨርሰቲ ተማሪዎች በፖሊስ ድብደባና እስራት እንደተፈፀመባቸው ዶቼ ቨለ ሬድዮ ተማሪዎቹን ዋቢ በማድረግ ዘግቧል።

ተማሪዎቹ ተራዝሟል ያሉትን የመመረቂያ ግዜን በመቃወም ሰልፍ የወጡ ሲሆን የትግራይ ክልል የፀጥታ ኃይሎች ከፍተኛ ድብደባ እና እንግልት እንደፈፀሙባቸው ተናግረዋል።

10 ተማሪዎች መታሰራቸውም ተገልጿል።

ተማሪዎቹ ዛሬ ረፋድ 4 ሰዓት ከመቐለ ዩኒቨርሲቲ አሪድ ግቢ ተነስተው ያሏቸውን ቅሬታዎች ለማሰማት ወደ መቐለ ከተማ ጎዳናዎች ሰላማዊ ሰልፍ ባደረጉበት ወቅት ነው ድብደባና እስራቱ የገጠማቸው።

ተማሪዎቹ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ለምን #ተገደዱ ?

በተለያዩ ችግሮች #ለዓመታት ትምህርታቸው ሲስተጓገል ቆይቶ ዘንድሮ 2016 ለመመረቅ እየተጠባበቁ የነበረ ቢሆንም ፤ ዩኒቨርሲቲው ሌላ ተጨማሪ ዓመት መማር እንደሚጠበቅባቸው ከገለፀላቸው በኃላ ነው ሰልፍ የወጡት።

ከሰላማዊ ሰልፉ በፊት ግን ለዩኒቨርሲቲው በተደጋጋሚ ቅሬታቸውን ማቅረባቸውን እና ከዩኒቨርሲቲው ምላሽ አለማግኘታቸውን ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል ገልጸዋል።

ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች   ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
 
            Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
╚═══════════╝