Get Mystery Box with random crypto!

'ዲግሪ ለመያዝ ስምንት ዓመት መቆየት ፍትሃዊ አይደለም! በዚህ ዓመት ልንመረቅ ይገባል!' የሚሉ ጥ | 🇪🇹ኢትዮ University

"ዲግሪ ለመያዝ ስምንት ዓመት መቆየት ፍትሃዊ አይደለም! በዚህ ዓመት ልንመረቅ ይገባል!" የሚሉ ጥያቄዎችን የያዙ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ዛሬ ጠዋት ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጋቸው ተሰምቷል።

"በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት የባከነውን የትምህርት ጊዜ ለማካካስ የሚሰጠው ትምህርት የፌደራል መንግሥት ባሰቀመጠው መመሪያ መሰረት እንዲከናወን" የዩኒቨርሲቲውን አስተዳደር በተደጋጋሚ መጠየቃቸውን ተማሪዎቹ ተናግረዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ተማሪዎቹ በጥር 2017 ዓ.ም ሊመረቁ እንደሚችሉ በዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች እንደተነገራቸው ተሰምቷል፡፡

በክልሉ ከተማ በተለምዶ የተባበሩት የሚባለው አካባቢ ጥያቄዎቻቸውን ሰላማዊ በሆነ መንገድ እያቀረቡ የነበሩት ተማሪዎቹ በጸጥታ ኃይሎች መበተናቸው ተነግሯል።

ፖሊስ አንዲት ሴትን (ተማሪ) ገፍትሮ አስፓልት ላይ ሲጥላት የሚያሳይ ቪዲዮ በማኅበራዊ ትስስር ገፆች ሲዘዋወር ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተመልክቷል፡፡ በተማሪዎቹ ላይ ጉዳት መድረስ አለመድረሱን ማረጋገጥ አልቻልንም፡፡

በጉዳዩ ላይ መቐለ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ትምህርት ሚኒስቴር የሚሉትን ወደፊት የምናደርሳችሁ ይሆናል፡፡

ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች   ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
 
            Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
╚═══════════╝