ተግባር ተኮር ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ ሆኖ የተለየው ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም. ወደ ትግበራ ይገባል፡፡
ተቋሙ ተግባር ተኮር ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ መሆን የሚያስችለውን የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ማጠናቀቁን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፋሪስ ደሊል (ዶ/ር) ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡
ግብርና፣ ኢንጅነሪንግና ቴክኖሎጂ፣ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ እንዲሁም የጤና ዘርፍ የዩኒቨርሲቲው የትኩረት መስኮች መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡
በአራቱም የዩኒቨርሲቲው ኮሌጆች የተግባር ትምህርት ለመስጠት የሚያስችሉ ቤተ-ሙከራዎች የመገንባትና የማጠናከር ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል፡፡
የመምህራን አቅም መገንባት፣ የተጨማሪ የዳታ ማዕከል ግንባታ፣ የዲጂታል ቴክኖሎጂ አቅም ማጎልበት እንዲሁም የሌሎች አስፈላጊ ግብዓቶች ማሟላት ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ፕሬዝዳንቱ ጠቅሰዋል፡፡ #ኢፕድ
ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1
@ethiouniversity1
@ethiouniversity1
╚═══════════╝