በአዲስ አበባ የ2015 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) ጉዳዩን አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
በመግለጫቸውም በዘንድሮዉ የ 2015 የትመህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናን አጠቃላይ 73 ሺህ 385 ተማሪዎች መፈተናቸውን አንስተዋል፡፡
ከነዚህ ውስጥም 70 ነጥብ 6 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች 50 እና ከዛ በላይ ውጤት ማምጣታቸውን ነው የተናገሩት፡፡
ተማሪዎች ውጤታቸውን ከደቂቃዎች በኋላ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ማኅበራዊ ትስስር ገጾች በሚለቀቁ ሊንኮች መመልከት እንደሚችሉም አስታውቀዋል፡፡
@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS