Get Mystery Box with random crypto!

'ቂም ' አቡነ ዘርአ ብሩክ ተወዳጆች ሆይ ኢትዮጵያዊው ፃድቅ ባለ 12 ክንፉ አባታችን አቡነ ዘ | Ethiopian orthodox mezemur

"ቂም "

አቡነ ዘርአ ብሩክ

ተወዳጆች ሆይ ኢትዮጵያዊው ፃድቅ ባለ 12 ክንፉ አባታችን አቡነ ዘርአ ብሩክ ከእለታት አንድ ቀን በቅዱስ ሚካኤል በአል ታህሳስ 12 ቀን እግዚአብሔር ነፍሳትን ከሲኦል እንዲያወጡ አዘዛቸው። አባታችንም የፈጣሪያቸውን ትእዛዝ ተቀብለው ወደ ሲኦል ወረዱ። ወደ አስፈሪው ሲኦል ገብተው በእሳት ሰንሰለት ለዘመናት በሰይጣን የታሰሩትን ስፍር ቁጥር የሌላቸውን ነፍሳት አገኙ።

ፃድቁም የእሳቱን ሰንሰለት በፈጣሪያቸው ስልጣን ፈተው እነዛን ምስኪን ነፍሳት ከስቃይ አወጧቸው። ግን አንድ አሳዛኝ ነገር ተመለከቱ። በሲኦል የተናቀች እና የወደቀች የአንድ የደግ መምህር የኤዎስጣቴኦስ ደቀ መዝሙር ስሙም አብሳዲ የሚባል ነፍስ ሰም ከፈትል እንደሚጣበቅ ተጣብቃ በሲኦል ባህር ውስጥ ስትሰቃይ አገኟት።

አቡነ ዘርአ ብሩክም ያቺን ነፍስ "እግዚአብሔር በዚህ የስቃይ ቦታ የጣለሽ በምን በደልሽ ነው" አሏት። ያቺም ምስኪን ነፍስ "በጥቂት ነገር እግዚአብሔር በዚህ የመከራ ቦታ ጣለኝ ሀጥያቴም ""ቂም ""
ናት" አለቻቸው። አባታችን አቡነ ዘርአ ብሩክም "በዚህ በመከራ ቦታ ምን ያህል ዘመን ኖርሽ" አሏት።

ምስኪኗ ነፍስም "በዚህ በመከራ ቦታ ከተቀመጥኩ 500 ዘመን ሆኖኛል" አለቻቸው። አባታችንም ይህን ነገር ከዚያች ነፍስ ሰምተው አዝነው "ከቅዱሳን ጋር በገነት ትኖሪ ዘንድ ነይ ውጪ" አሏት"

ያን ጊዜ ከሞት ጉድጓድ አውጥተው በዚያች ቀን ከሲኦል ከወጡት ነፍሳት ጋር በእግዚአብሔር ፊት አቆሟ። እግዚአብሔርም ያችን ነፍስ በፃድቁ ቃል ኪዳን በገነት ውኃ ተጠምቃ ከገብበት መውጣት፣ ካገኙ ማጣት ከሌለባት ገነት እንደገባች ድንቅ ገድላቸው ይነግረናል።

ቸል የምንለው ቂም ምንኛ የነፍስ እዳና ፍዳ እንደሚያመጣብን ልብ እንበል ።

#በቀሲስ_ሄኖክ_ወልደ-ማርያም

ሼር በማድረግ ለወዳጆ አዳርሱ!
@finote_tsidk
@finote_tsidk