2022-07-30 11:02:03
“‘ምስጋና ለአላህ ይገባው’ በላቸው።”»(ሉቅማን፡25)
አላህ በህይወት አቆይቶ ዛሬ አንድ ብሎ ለጀመረው 1444 ዓመተ ሂጅራ አደረሰን።አላህ ሆይ! ቁጥር ስፍር የሌለው ምስጋናችን ይድረስህ። አስተውለን ካየን በየእለቱ አንተን የምናመሰግንበት እጅግ ብዙ ምክንያቶች አሉን።በተለይ እንደ ሙስሊም ኢትዮጵያዊ ሌላው ቢቀር ብዙ የተንገላታንበትና ዋጋ የከፈልንለት የመጅሊስ ጉዳይ ሊከፋፍሉንና ደም እንድንፋሰስ የተመኙና አሰፍስፈው ሲጠብቁ የነበሩት አካላት እንዳሰቡት ሳይሆን በሰላም መስመር በመያዙ ብቻ እንኳን ብዙ ልናመሰግንህ ይገባናል። አልሀምዱሊላህ!
ነቢያችን(ሰ. ዐ. ወ) «ሰውን ያላመሰገነ አላህን አያመሰግንም።» እንዳለት ከአላህ በታች አዎንታዊ ሚና ለነበራቸው ሁሉም ምስጋናዬም ይድረስ።
ደስታችን ዘላቂ እንዲሆንና እንዲጨመርልን መንገዱ ማመስገን ነው። አላህ(ሱ.ወ) እንዲህ ይለናል፦
وَإِذْ تَأَذَّنَ رَبُّكُمْ لَئِن شَكَرْتُمْ لَأَزِيدَنَّكُمْ ۖ وَلَئِن كَفَرْتُمْ إِنَّ عَذَابِي لَشَدِيدٌ [١٤:٧]
«ጌታችሁም «ብታመሰግኑ በእርግጥ እጨምርላችኋለሁ ብትክዱም (እቀጣችኋለሁ) ቅጣቴ በእርግጥ ብርቱ ነውና» በማለት ባስታወቀ ጊዜ (አስታውሱ)፡፡»(ኢብራሂም፡7)
“And [remember] when your Lord proclaimed, 'If you are grateful, I will surely increase you [in favor]; but if you deny, indeed, My punishment is severe.'”(Qura’n ,Ibrahim:7)
«ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን፡፡»(አስ-ሳፋት፡182)
662 views08:02