Get Mystery Box with random crypto!

ኢ.ዜ.አ

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopianewsagency — ኢ.ዜ.አ
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopianewsagency — ኢ.ዜ.አ
የሰርጥ አድራሻ: @ethiopianewsagency
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 434
የሰርጥ መግለጫ

The Ethiopian News Agency dispatches text news, audio and video stories about local and international events to media enterprises and the public.
www.ena.et
facebook.com/ethiopianewsagency
Call
1(202) 205-9932 Ext 13

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-07-23 19:59:32 ቅዳሜ ሐምሌ 16/2014 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ የዓለም ጤና ድርጅት ዛሬ የዝንጀሮ ፈንጣጣን "የዓለም አጣዳፊ የጤና ቀውስ" በማለት እንደፈረጀው የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድኻኖም አስታውቀዋል። ዶ/ር ቴዎድሮስ በሽታውን "አጣዳፊ የዓለም የጤና ቀውስ" በማለት ያወጁት፣ ሐሙስ'ለት በጉዳዩ ላይ የመከረው የድርጅቱ የአጣዳፊ በሽታዎች ኮሚቴ ሙሉ ስምምነት ላይ ሳይደርስ እንደሆነ ተገልጧል። ከጥር ወዲህ በ75 አገራት ከ16 ሺህ 500 በላይ ሰዎች የዝንጀሮ ፈንጣጣ ቫይረስ እንደተገኘባቸው የድርጅቱ መረጃ ያመለክታል። የኢትዮጵያ ጤና ሚንስቴር ቫይረሱ በአገሪቱ ስለመገኘቱ እስካሁን ሪፖርት አላደረገም።

2፤ በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር የኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት እና ሕወሃት ሊያደርጉት ባሰቡት ድርድር ዙሪያ ለመነጋገር ከነገ እስከ ሐምሌ 25 ድረስ ባሉት ቀናት ወደ ኢትዮጵያ ሊያቀኑ መሆኑን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል። ሐመር በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው፣ በሰሜኑ ጦርነት የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን የፈጸሙ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑ እንደሚጠይቁ ተገልጧል። ሐመር ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ግብጽን እና የተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶችን እንደሚጎበኙና በሕዳሴ ግድብና በኢትዮ-ሱዳን ውዝግብ ዙሪያ ጭምር ከአገራቱ ባለሥልጣናት ጋር ይወያያሉ።

3፤ የፌደራል ጸጥታና ደኅንነት ግብረ ኃይል በአማራ ክልል 5 ሺህ 804 "ጽንፈኛ" ያላቸውን የፋኖ ሚሊሽያ አባላት በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያደረገባቸው መሆኑን ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። በቁጥጥር ስር ውለዋል የተባሉት የፋኖ አባላት፣ ከመደበኛ ጸጥታ ተቃማት እውቅና ውጭ ወጣቶችን በመመልመል፣ በኅቡዕ በማሰልጠን፣ መሳሪያ በማስታጠቅ፣ ንጹሃንን በመግደል፣ በማፈናቀልና ሁከት በመፍጠር የተጠረጠሩ መሆናቸውን ግብረ ኃይሉ ጠቅሷል። ግብረ ኃይሉ በአማራ ክልልና የፌደራል ባለሥልጣናት ላይ ጥቃት ለማድረስና መንግሥት ገልብጠው የሽግግር መንግሥት ለማቋቋም አሲረዋል ያላቸውን 14 የፋኖ አባላት ማሰሩንም ገልጧል።

4፤ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ባለፉት ጥቂት ወራት በታጣቂዎች ጥቃት 1 ሺህ 106 ንጹሃን እና 28 የመንግሥት አስተዳደር ሃላፊዎች እንደተገደሉ የዞኑ አስተዳዳሪ ገመቺስ ደበላ ለክልሉ ምክር ቤት ጉባዔ ባቀረቡት ሪፖርት መግለጣቸውን ሰምተናል። በታጣቂዎች ጥቃትና ባካባቢው ባለው ግጭት ዞኑ ከ3 ቢሊዮን ብር በላይ የንብረት ውድመት እንደደረሰበት ሪፖርቱ ጠቅሷል። በክልሉ ሰሜን ሸዋ ዞን ደሞ ታጣቂዎች በፈጠሩት የጸጥታ ችግር 195 ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል ተብሏል። የክልሉ ምክር ቤት ለቀጣዩ ዓመት ለጸጥታ ጥበቃ የበጀተው 400 ሚሊዮን ብር ነው።

5፤ አፍሪካ ኅብረት የዩክሬን የእህል ምርቶች ከዩክሬን ወደቦች ለዓለም ገበያ እንዲቀርቡ ሩሲያና ዩክሬን የደረሱበትን ስምምነት እንደሚያድንቅ ባወጣው መግለጫ ገልጧል። በተመድ እና ቱርክ አደራዳሪነት በተደረሰው ስምምነት መሠረት፣ የዩክሬን የእህል ምርቶች በቅርቡ ለውጭ ገበያ ይቀርባሉ ተብሏል። በጦርነቱ በተዘጉት የዩክሬን ወደቦች 20 ሚሊዮን ቶን የምግብ ጥራጥሬ የተከማቸ ሲሆን፣ እህሉ ለገበያ መቅረቡ የአፍሪካ አገራትን የምግብ እጥረትና የምግብ ዋጋ ውድነት ያቃልላል ተብሎ ታምኖበታል።

6፤ ቻይና ሰራሹ አዲሱ ሲ919 የመንገደኞች አውሮፕላን የሙከራ በረራዎቹን ሙሉ በሙሉ በስኬት ማጠናቀቁን ሮይተርስ ዘግቧል። አዲሱ አውሮፕላን ከአገሪቱ የሲቪል አቬሽን ተቆጣጣሪ ባለሥልጣን በቅርቡ የበረራ ፍቃድ ለማግኘት የመጨረሻው ደረጃ ላይ መድረሱን ዘገባው አመልክቷል። አውሮፕላኑ የአሜሪካውን ቦይንግ-737 ማክስ እና የአውሮፓውን ኤርባስ-320 እንዲቀናቀን ተደርጎ የተሰራ ነው።

@Ethiopianewsagency (ኢዜአ)
147 viewsedited  16:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-23 09:05:35 ቅዳሜ ሐምሌ 16/2014 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ ዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት አይ ኤም ኤፍ ኢትዮጵያ የተራዘመ ብድር ለማግኘት ባቀረበችው ጥያቄ ላይ በመጭው በመስከረም ወር ድርድር ሊጀመር እንደሚችል ጠቁሟል። ድርጅቱ ይህን ጥቆማ የሰጠው፣ የኢትዮጵያ አበዳሪ አገሮች ኮሚቴ ሰኞ'ለት ባደረገው ስብሰባ ላይ ነው። የመንግሥት እና ድርጅቱ ድርድር ባለፈው መስከረም እንዲጠናቀቅ ታስቦ፣ ወዲያው መቋረጡ ይታወሳል። የአበዳሪ አገሮች ኮሚቴ በሰኞ'ለቱ ስብሰባው፣ ኢትዮጵያ በውጭ ብድር አከፋፈሏ ላይ ሽግሽግ እንዲደረግላት ባቀረበችው ጥያቄ ላይ ምን ዓይነት ውሳኔ እንዳሳለፈ አልታወቀም።

2፤ አልሸባብ በኢትዮጵያ እና ሱማሊያ ድንበር ላይ በፈጸመው ጥቃት ሦስት ሰላማዊ ሰዎችን እና 14 የሱማሌ ክልል ልዩ ኃይሎችን መግደሉን ከአንድ የኢትዮጵያ ወታደራዊ አዛዥ ሰምቻለሁ በማለት ሮይተርስ ዘግቧል። በተኩስ ልውውጡ 64 የቡድኑ ታጣቂዎችም እንደተገደሉ አዛዡ ጠቁመዋል። ቡድኑ ጥቃቱን የፈጸመው፣ አንድ አዛዡ በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ ሕዋስ ለማቋቋም ገብተው ከተገደሉበት በኋላ እንደሆነ ተገልጧል። ሱማሌ ክልል ስለ ክስተቱ ያለው ነገር የለም።

3፤ የምሥራቅ አፍሪካ ኢኮኖሚ ማኅበረሰብ ሱማሊያ የማኅበረሰቡ አባል ለመሆን ያላትን ዝግጁነት የሚያጠና ቡድን ለመላክ መወሰኑን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የኢኮኖሚ ማኅበረሰቡ ይህን የወሰነው፣ የአባል አገራቱ መሪዎች በታንዛኒያ አሩሻ ሰሞኑን ባደረጉት ጉባዔ ላይ ነው። የሱማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሐመድ በጉባዔው ላይ በእንግድነት ተገኝተው፣ ሱማሊያ የኢኮኖሚ ማኅበረሰቡን ለመቀላቀል ያላትን ዝግጁነት አስረድተዋል።

4፤ የዩክሬን እህል ምርት ከየክሬኑ ጥቁር ባሕር ወደቦች ወደ ዓለም ገበያ እንዲወጣ የሚያስችል ስምምነት ሩሲያ እና ዩክሬን ትናንት መፈራረማቸውን ሮይተርስ ዘግቧል። የተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ የስምምነቱ ተግባራዊነት አፍሪካን ጨምሮ በበርካታ ታዳጊ አገራት የምግብ ዋጋ እንዲቀንስ ያስችላል ብለዋል። ወደቦቹ እንዲከፈቱ ሁለቱን አገሮች ያስማሙት፣ ተመድ እና ቱርክ ናቸው። በዩክሬን ወደቦች ከ20 ሚሊዮን ቶን በላይ ጥራጥሬ ተከማችቷል።

5፤ ሜታ ኩባንያ ኬንያ ነሐሴ ሦስት ከምታካሂደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ዙሪያ የተሰራጩ 37 ሺህ ሐሰተኛ መረጃዎችንና የጥላቻ ንግግሮችን ከማኅበራዊ ትስስር መተግበሪያዎቹ ማስወገዱን ገልጧል። ኩባንያው በማኅበራዊ ትስስር ገጾቹ ግጭት ቀስቃሽ መልዕክቶች እንዳይሰራጩ ጥብቅ ቁጥጥር እያደረገ እና በፌስቡክ፣ ኢንስታግራምና ሜሴንጀር መተግበሪያዎቹ ላይ የኬንያዊ ታዋቂ ሴቶችንና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን ደኅንነት የሚያስጠብቁ ርምጃዎችን መውሰዱን ጨምሮ ገልጧል።

6፤ የዓለም ጤና ድርጅት ታዳጊ አገራት ለአዲሱ የወባ ክትባት መግዣ የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት እንዲያመለክቱ አሳስቧል። ድርጅቱ በመጀመሪያው ዙር ክትባቱን ለኬንያ፣ ማላዊና ጋና ለማከፋፈል ተዘጋጅቷል። ከፋፍል መሆኑን አሶሴትድ ፕሬስ ዘግቧል። ክትባቱ ወባ በሽታን የመከላከል አቅሙ 30 በመቶ ሲሆን፣ ቢል ጌትስ ፋውንዴሽን ይህንኑ በመጥቀስ፣ ለክትባቱ ምርትና ሥርጭት ቀጥተኛ የገንዘብ ድጋፉን ማቋረጡን አሶሴትድ ፕሬስ ዘግቧል። የክትባቱ አምራች ኩባንያም ለቀጣዮቹ ስድስት ዓመታት በዓመት የሚያመርተው 15 ሚሊዮን ዶዝ ብቻ እንደሆነ ገልጧል።

@Ethiopianewsagency (ኢዜአ)
130 viewsedited  06:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 22:10:46 ሐሙስ ሐምሌ 14/2014 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ የደቡብ ክልል ምክር ቤት ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ጉባዔ መጀመሩን የክልሉ ኮምንኬሽን ቢሮ ገልጧል። የክልሉ መንግሥት የ2014 ዓ፣ም በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርቱን እና የቀጣዩን ዓመት በጀት ጉባዔው እንዲያጸድቅለት አቅርቧል። ጉባዔው በክልልነት የመደራጀት ጥያቄዎችን በአጀንዳነት አልያዘም። ሆኖም የምክር ቤቱ አፈ ጉባዔ ፋጤ ሰርመሎ በጉባዔው መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ምክር ቤቱ ቀደም ሲል ለቀረቡለት በክልልነት የመደራጀት ጥያቄዎች ሕጋዊ ምላሽ ለመስጠት እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን አውስተዋል።

2፤ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ለጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የፈቀደውን ዋስትና እንዲያነሳ ዓቃቤ ሕግ ሰኞ'ለት በጽሁፍ የጠየቀው ከመከላከያ ሠራዊት ደብዳቤ ከደረሰው በኋላ እንደሆነ የተከሳሹ ጠበቃ ኄኖክ አክሊሉ ለአገር ውስጥ ዜና ምንጮች ተናግረዋል። የፌደራሉ ዓቃቤ ሕግ መከላከያ ሠራዊት ጋዜጠኛው በተደጋጋሚ በመጽሄቱ ባተማቸው መጣጥፎች በሠራዊቱ ላይ ወንጀሎችን ፈጽሟል የሚል ውንጀላ የያዘ ደብዳቤ እንደላከለት ገልጧል። መከላከያ ሠራዊት በደብዳቤው ተከሳሹ ከእስር እንዳይፈታ ማስጠንቀቁን የገለጡት ጠበቃው፣ በጋዜጠኛው ላይ የራሴን ርምጃ እወስዳለሁ በማለት መዛቱን ጠቅሰዋል።

3፤ የሩሲያው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሰርጌ ላቭሮቭ በመጭው ማክሰኞና ረቡዕ ኢትዮጵያን እንደሚጎበኙ በአዲስ አበባ የሩሲያ ኢምባሲ አስታውቋል። ላቭሮቭ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ፣ ኡጋንዳን፣ ግብጽንና ዲሞክራሲያዊት ኮንጎ ሪፐብሊክን ይጎበኛሉ። የሩሲያና ዩክሬን ጦርነት ከተቀሰቀሰ ወዲህ፣ ላቭሮቭ አፍሪካን ሲጎበኙ ያሁኑ የመጀመሪያቸው ነው። የተመድ ጠቅላላ ጉባዔ የሩሲያን የዩክሬን ወታደራዊ ዘመቻ በማውገዝ ከጥቂት ወራት በፊት የውሳኔ ሃሳብ ሲያሳልፍ፣ ኢትዮጵያ ከድምጽ አሰጣጥ ሂደቱ ራሷን ማግለሏ ይታወሳል።

4፤ የሱማሊያው አልሸባብ ታጣቂዎች በሱማሊያ-ኢትዮጵያ ድንበር ትናንት ጥቃት እንደፈጸሙ የሱማሊያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ታጣቂዎቹ ጥቃቱን የፈጸሙት፣ በሳውዝ ዌስት ግዛት በባኮል አውራጃ በሁለት የድንበር ከተሞች ላይ ባሉ ጸጥታ ኃይሎች እንደሆነ ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። በጥቃቱ እና በተኩስ ልውውጡ ምን ያህል ጉዳት እንደደረሰ አልታወቀም። ከነጻ ምንጭ ባይረጋገጥም አልሸባብ ሁለቱን ከተሞች ተቆጣጥሬያለሁ ብሏል።

5፤ ዛሬ አሩሻ ታንዛኒያ የገቡት የሱማሊያው ፕሬዝዳንት ሞሐመድ በምሥራቅ አፍሪካ የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ የመሪዎች ጉባዔ ላይ ማኅበረሰቡ አገራቸውን በአባልነት እንዲቀበል በድጋሚ እንደሚጠይቁ ቤተ መንግሥታቸው አስታውቋል። ሱማሊያ ከስድስት ዓመታት በፊት የማኅበረሰቡ አባል ለመሆን ያቀረበችውን ጥያቄ፣ ማኅበረሰቡ በአገሪቱ ያለውን ግጭትና ጠንካራ ተቋማት የሌሏት መሆኗን በመጥቀስ አልተቀበላትም ነበር። ሆኖም ማኅበረሰቡ በግጭት ስትታመስ የከረመችውን ደቡብ ሱዳንንና ዲሞክራያዊት ኮንጎ ሪፐብሊክን በመቀበሉ፣ ሱማሊያ ጥያቄዋን በድጋሚ እንድታቀርብ ምክንያት ሆኗታል ተብሏል።

6፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 52 ብር ከ1031 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 53 ብር ከ1452 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 59 ብር ከ5858 ሳንቲም፣ መሸጫው 60 ብር ከ7775 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ53 ብር ከ0878 ሳንቲም ሲገዛ እና በ54 ብር ከ1496 ሳንቲም ሲሸጥ ውሏል።

@Ethiopianewsagency (ኢዜአ)
144 viewsedited  19:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 21:57:37 ማክሰኞ ሐምሌ 12/2014 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ ትግራይ ክልልን የሚያስተዳድረው ሕወሃት የኢትዮጵያ መንግሥት በትግራዩ ጦርነት የወደሙ መሠረተ ልማቶችን መልሶ የመገንባቱን ሃላፊነት በተናጥል ውሳኔ ለተመድ የፕሮጀክቶች አገልግሎት ቢሮ መስጠቱን እንደሚቃወም ተናገረ። መንግሥት የትግራይን መልሶ ግንባታ የተመድ ቢሮ ሃላፊነት ወስዶ እንዲመራው ባለፈው ሳምንት ስምምነት ላይ ሲደርስ፣ ሕወሃት አንዳችም የሚያውቀው ነገር እንደሌለ የድርጅቱ ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳ ተናግረዋል። ጌታቸው የትግራይ መልሶ ግንባታ ሥራ ከመጀመሩ በፊት፣ በአጠቃላይ በመልሶ ግንባታው መርሃ ግብር ላይ ሁሉም ባለድርሻዎች መግባባት ላይ መድረስ አለባቸው ብለዋል።

2፤ የስፔኑ የነፍስ አድን ድርጅት ኤም ኤስ ኤፍ ዋና ዳይሬክተር ፓውላ ጊል በትግራዩ ጦርነት ወቅት በተገደሉ ሦስት የድርጅቱ ነፍስ አድን ሠራተኞች ዙሪያ ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር ለመነጋገር አዲስ አበባ እንደገቡ ድርጅቱ አስታውቋል። ሃላፊዋ ወደ ትግራይ ክልል በማቅናት፣ የትግራይ ተወላጆች የሆኑትን የሁለቱን ሟቾች ቤተሰቦች እንደሚያነጋግሩ እና ድርጅቱ በግድያው ዙሪያ እስካሁን የደረሰበትን የውስጥ ምርመራ ውጤት እንደሚያጋሩ ድርጅቱ ጨምሮ ገልጧል። ስፔናዊቷ ማሪያ ኸርናንዴዝ፣ ቴዎድሮስ ገ/ማርያም እና ዮሃንስ ሃለፎም አምና ሰኔ ወር ትግራይ ውስጥ የተገደሉት ለነፍስ አድን ተልዕኮ በድርጅቱ ተሽከርካሪ በመጓዝ ላይ ሳሉ ነበር።

3፤ የ"ፍትህ" መጽሄት ባለቤትና ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ትናንት ዓቃቤ ሕግ በመሠረተበት ክስ ላይ ለከፍተኛው ፍርድ ቤት መቃወሚያ ማቅረቡን ቤተሰቦቹ አስታውቀዋል። ችሎቱም ዓቃቤ ሕግ ምላሹን ለሐምሌ 20 እንዲያስገባ በማዘዝ፣ ለሐምሌ 20 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተከሳሹ ባቀረበው የዋስትና ጥያቄ ላይ ነገ ውሳኔ እንደሚሰጥ ይጠበቃል። ከፍተኛው ፍርድ ቤት ቀደም ሲል ለተከሳሹ የፈቀደውን ዋስትና ጠቅላይ ፍርድ ቤት ማገዱ ይታወሳል።

4፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 52 ብር ከ0890 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 53 ብር ከ1308 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 59 ብር ከ5746 ሳንቲም፣ መሸጫው 60 ብር ከ7661 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ52 ብር ከ9172 ሳንቲም ሲገዛ እና በ53 ብር ከ9755 ሳንቲም ሲሸጥ ውሏል።

5፤ የአፍሪካ ልማት ባንክ ለአሕጉራዊው የአፍሪካ ነጻ ንግድ ቀጠና 11 ሚሊዮን ዶላር መለገሱን አስታውቋል። ባንኩ ገንዘቡን የለገሰው በነጻ ንግድ ቀጠናው ውስጥ በአባል አገራት መካከል የሚካሄዱ የንግድ ልውውጦችን ይበልጥ ማጎልበት እንዲቻል ነው። ባንኩ አሕጉራዊው ነጻ ንግድ ቀጠና ከሁለት ዓመት በፊት በይፋ ሲታወጅ አምስት ሚሊዮን ዶላር መለገሱ ይታወሳል። የነጻ ንግድ ቀጠናውን ተግባራዊ በማድረግ ረገድ፣.ሁሉም አባል አገራት እኩል እየተራመዱ እንዳልሆነ በተደጋጋሚ ተገልጧል።

@Ethiopianewsagency (ኢዜአ)
174 viewsedited  18:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 08:45:03 ማክሰኞ ሐምሌ 12/2014 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ የትግራዩ ሕወሃት ከፌደራል መንግሥት ጋር ለሚያደርገው ድርድር ተደራዳሪ ቡድን ማዋቀሩን የፈረንሳዩ ዜና ወኪል የሕወሃት ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳን ጠቅሶ ዘግቧል። ሆኖም ሕወሃት ከመንግሥት ጋር ድርድር የሚቀመጠው በአፍሪካ ኅብረት አደራዳሪነት ሳይሆን በኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ አማካኝነት እንደሆነ እና የምዕራባዊ ትግራይ አካባቢዎችን ለድርድር እንደማያቀርብ ጌታቸው መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል። የሕወሃት ተደራዳሪ ቡድን አባላት እነማን እና ስንት እንደሆኑ ግን ዘገባው አልጠቀሰም።

2፤ ፈረንሳይ እና ቻይና የሚመሩት የዓለማቀፍ አበዳሪዎች ኮሚቴ የኢትዮጵያን የውጭ እዳ መክፈያ ጊዜ ለማሸጋሸግ ትናንት እንደሚሰበሰብ ቀደም ሲል ተዘግቦ ነበር። ኮሚቴው በጉዳዩ ላይ ስለመምከሩ ወይም መክሮ ከሆነ ምን ውሳኔ እንዳሳለፈ ግን ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ የታወቀ ነገር የለም። አንድ የመንግሥት ሃላፊ ኢትዮጵያ ባሁኑ ወቅት በዓመት እየከፈለችው ያለችው የውጭ ብድር ከሁለት ቢሊዮን ዶላር ያነሰ መሆኑን እና የእዳ መክፈያዋ ጊዜ መሸጋሸጉ ግን ተጨማሪ ብድር እንድታገኝ ዕድል ሊፈጥርላት እንደሚችል ተናግረዋል።

3፤ መንግሥት በዛምቢያ እስር ቤቶች የታሰሩ ኢትዮጵያዊያን ዜጎችን በሳምንቱ መጨረሻ ገደማ ወደ አገራቸው ሊመልስ መሆኑን ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል። ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ደመቀ ከአፍሪካ ኅብረት ሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ በተጓዳኝ በዛምቢያ ከሚገኙ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ አባላት ጋር ባደረጉት ውይይት፣ ቁጥራቸው ያልታወቀ ኢትዮጵያዊያን በአገሪቱ እስር ቤቶች እንደሚገኙ ተወስቷል። ኢትዮጵያዊያን ዛምቢያ ውስጥ የታሰሩት፣ በሕገወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች አማካኝነት ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመሻገር ጉዞ ላይ ሳሉ ነው። ኢትዮጵያ በዛምቢያ ኢምባሲ ወይም ቆንስላ የላትም።

4፤ ፍርድ ቤት በሙስና ተጠርጣሪው የአዲስ አበባ ከተማ የቴክኒክ ሥልጠናና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ሃላፊ እና የከተማዋ ምክር ቤት አባል ሙሉቀን ሃብቱ ላይ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ መፍቀዱን አመልክቷል። ሙሉቀን ባለፈው ዓርብ ያለመከሰስ መብታቸውን ከተነሳ በኋላ ነበር በቁጥጥር ስር የዋሉት። መርማሪ ፖሊስ ግለሰቡ የከተማዋ አስተዳደር ከ10 ቀን በፊት ባወጣው የጋራ መኖሪያ ቤቶች እጣ ላይ በተፈጸመ ማጭበርበር፣ ተጠርጣሪው ሥልጣናቸውን ያላግባብ በመጠቀምና በሙስና ወንጀሎች እንደጠረጠራቸው ለችሎቱ አስረድቷል።

5፤ በሱዳኗ ብሉ ናይል ግዛት ካለፈው ሳምንት ጀምሮ የተቀሰቀሰው የጎሳ ግጭት ወደ ሰሜናዊቷ ከሰላ ግዛት እንደተዛመተ የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ባለፉት ቀናት በብሉ ናይል ግዛት በሐውሳ እና በርታ ጎሳዎች መካከል በተቀሰቀሰው ግጭት፣ ከ65 በላይ ሰዎች እንደተገደሉ ተነግሯል። የአገሪቱ ወታደራዊ መንግሥት በብሉ ናይል እና ከሰላ የተቀሰቀሱትን የጎሳ ግጭቶች የሚያጣሩ ቡድኖች አቋቁሟል።

@Ethiopianewsagency (ኢዜአ)
173 viewsedited  05:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-16 21:56:56 ቅዳሜ ሐምሌ 9/2014 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ ፌደሬሽን ምክር ቤት ለውስን ዓላማ የሚደረግ የበጀት ድጎማን እና የፌደራል መሠረተ ልማትን ፍትሃዊ ሥርጭት ለመከታተል የሚያስችለውን ሥርዓት ለማስፈጸም የተረቀቀ ደንብ ማጽደቁን አስታውቋል። ደንቡ በክልሎች የመሠረተ ልማት ግንባታ በሚያካሂዱ የፌደራል ተቋማት እና ፌደራል መንግሥት ለክልሎች በሚመድበው ውስን ዓላማ ያላቸው ድጎማዎች ላይ ተግባራዊ የሚሆን ነው።

2፤ የመንግሥት የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል በደቡብ ክልል በክልልነት በመደራጀት ጥያቄ ስም ግጭት እና አመጽ የሚቀሰቅሱ አካላትን እንደማይታገስ ትናንት ማምሻውን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። የደቡብ ክልል መንግሥት ዞኖቹን እንደገና ለማዋቀር ጥረት ላይ መሆኑን የገለጠው ግብረ ኃይሉ፣ የጌዲኦ ዞን ጥያቄን በኃይል ለማስፈጸም በኅቡዕ ተደራጅተው የሚንቀሳቀሱ አካላት እንዳሉ ደርሼበታለሁ ብሏል። ግብረ ኃይሉ ጨምሮም፣ እነዚሁ አካላት በማኅበራዊ ትስስር ዘዴዎች ሐሰተኛ መረጃዎችን እያሰራጩ እና የቤት ለቤት ቅስቀሳ እያደረጉ እንደሚገኙ ገልጧል።

3፤ ታጣቂዎች በደቡብ ክልል ቡርጂ ልዩ ወረዳ ባደረሱት ጥቃት አራት ሰዎች ተገድለው አምስቱ እንደቆሰሉ ቪኦኤ የአካባቢውን ምንጮች ጠቅሶ ዘግቧል። የታጣቂ ቡድኑ ታጣቂዎች በአጎራባቹ አማሮ ልዩ ወረዳ ላይ ጭምር በፈጸሙት ተመሳሳይ ጥቃት፣ አንድ አርሶ አደር ገድለው በርካታ እንስሳትን ዘርፈዋል ተብሏል። ታጣቂ ቡድኑ ከቡርጂ ወረዳ አጎራባች ከኦሮሚያው ምዕራብ ጉጂ ዞን የሚነሳ እንደሆነ ተገልጧል።

4፤ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የከተማዋን ማቋቋሚያ ቻርተር ያሻሻለ ረቂቅ እንዳዘጋጀ ገለፀ። የተሻሻለው ረቂቅ ቻርተር፣ በሕግ ማውጣት፣ ማስፈጸም እና መተርጎም ሂደት ቅሬታ ይቀርብባቸው በነበሩ አንቀጾች እና በከተማዋ የገቢ ክፍፍል ጉዳይ ላይ የማሻሻያ ሃሳቦችን ይዟል። ረቂቅ ቻርተሩ የከተማዋ ፖሊስ ተጠሪነት ለከተማዋ አስተዳደር እንዲሆንም ሃሳብ አቅርቧል። ረቂቅ ቻርተሩ ሥራ ላይ የሚውለው፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ካጸደቀው ነው።

5. አሀዱ ባንክ 23ኛው የግል ባንክ ሆኖ ዛሬ በይፋ ተመርቆ ስራ ይጀምራል::
አሃዱ ባንክ በ564 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል 10 ሺህ ባለ ድርሻዎችን ይዞ ዛሬ ወደ ባንክ ገበያ መቀላቀሉን አስታውቋል። ብሄራዊ ባንክ አዲስ ለሚቋቋሙ ባንኮች ያስቀመጠው ዝቅተኛው የተከፈለ ካፒታል መጠን 500 ሚሊዮን ብር ሲሆን፣ ባንኩ ግን በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት በአዲሱ የብሄራዊ ባንክ መመሪያ መሠረት ካፒታሉን ወደ 5 ቢሊዮን ብር እንደሚያሳድግ ገልጧል። ባንኩ እስከ መስከረም ቅርንጫፎቹን 50 እንደሚያደርስ እና ወደፊት 70 በመቶ ቅርንጫፎቹ በገጠሮች ከፍቶ ዝቅተኛ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተናግሯል።

6፤ በኬንያ ጉብኝት ላይ ያሉት የሱማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐመድ ከኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር የንግድ እና ዲፕሎማሲያዊ ስምምነቶችን መፈራረማቸውን የኬንያ ጋዜጦች ዘግበዋል። በስምምነቱ መሠረት ኬንያ ታግዶባት የቆየውን የጫት ምርቷን ወደ ሱማሊያ መላክ የምትጀምር ሲሆን፣ ሱማሊያ ደሞ የአሳ ምርቶችን ወደ ኬንያ ትልካለች። የኬንያ አየር መንገድም አቋርጦት የነበረውን የሞቃዲሾ በረራውን እንደገና ይጀምራል።

7፤ በሱማሊያ የአፍሪካ ኅብረት ሰላም ተልዕኮ በሱማሊያ 160 ናይጀሪያዊያን ፖሊሶችን ማሰማራቱን አስታውቋል። ፖሊሶቹ ቀደም ሲል ተልዕኳቸውን ያጠናቀቁ የናይጀሪያ ፖሊሶችን የሚተኩ ናቸው። በተመድ ጸጥታው ምክር ቤት ውሳኔ መሠረት፣ የሱማሊያ የሰላም ተልዕኮ ለአገሪቱ ፖሊስ ሠራዊት ድጋፍ የሚሰጡ አንድ ሺህ አርባ ፖሊሶች ይኖሩታል። በሱማሊያ ፖሊስ ኃይል ያሠማሩት፣ ኬንያ፣ ናይጀሪያ፣ ጋና፣ ኡጋንዳ፣ ዛምቢያ እና ሴራሊዮን ናቸው።

@Ethiopianewsagency (ኢዜአ)
186 viewsedited  18:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 23:35:56 #መረጃ!

አመሻሹን ከ1 ሰአት ጀምሮ የኦነግ አሸባሪዎች በአውላል ቆሪ ሜዳ በኩል አድርገው ተኩስ መክፈታቸውና የኤፍራታና ግድም ወረዳ ቀበሌ ወደሆኑት ሸህ ሰማንና በረሀ ቀበሌዎች ከባድ መሳሪያ እየተኮሱ ማምሸታቸውን ከነዋሪዎች የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ በአሁኑ ሠአት ተኩሱ የተወሰነ የቀነሰና አልፎ አልፎ የሚሠማ ሲሆን ከነዋሪዎቹ ሴቶችና ህፃናት እንዲሁም አቅመ ደካሞች ስጋት ስላደረባቸው ወደአጎራባች አካባቢዎች ለመሄድ መገደዳቸውን ገልፀዋል፡፡

በስፍራው ምንም አይነት የፀጥታ ሀይል አለመኖሩም ተነግሯል!

@Ethiopianewsagency (ኢዜአ)
185 viewsedited  20:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 21:36:13 ዓርብ ሐምሌ 8/2014 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የምክር ቤቱን አባል እና የከተማዋ የቴክኒክ ሥልጠናና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ሃላፊ መሉቀን ሃፍቱን ያለመከሰስ መብት በአብላጫ ድምጽ ማንሳቱን አስታውቋል። ሙሉቀን በፍትህ ሚንስቴር ጥያቄ ያለ መከሰስ መብታቸው የተነሳው፣ አስተዳደሩ ባለፈው ሳምንት ባወጣው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ላይ ከተፈጸመው የመረጃ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ ነው። አስተዳደሩ በዕጣው ላይ ማጭበርበር እንደተፈጸመ አረጋግጫለሁ በማለት ረቡዕ'ለት ዕጣውን መሉ በሙሉ ሰርዟል።

2፤ የአዲሱ አማራ ባንክ እመርታ ሌሎች ባንኮች ለሠራተኞቻቸው የደመወዝ ጭማሪና ጥቅማ ጥቅም መስጠትን ጨምሮ ሌሎች ማሻሻያዎችን እንዲያደርጉ እንዳስገደዳቸው ተመልክተናል። ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክና ከግል ባንኮች የቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጆችንና የብድር ባለሙያዎችን ጨምሮ በርካታ የባንክ ሠራተኞች አማራ ባንክን ተቀላቅለዋል። ባንኩ 70 መነሻ ቅርንጫፎቹን አሁን 100 ማድረሱን የባንኩ ሃላፊዎች ተናግረዋል። በ6.5 ቢሊዮን ብር ካፒታል የተቋቋመው ባንኩ 50 በመቶ ባለድርሻዎቹ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ሲሆኑ፣ 20 በመቶዎቹ ደሞ ከአማራ ክልል ናቸው።

3፤ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ባለሙያዎች ማኅበር መንግሥት የዜጎችን በሕይወት የመኖር መብት እንዲከበር ዘገባዎችን የሚሰሩ ጋዜጠኞችን ማንገላታትና ማሰር እንዲያቆም ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። ማኅበሩ መንግሥት ተጠርጣሪ ጋዜጠኞችን አፍኖ መሰወርና በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ዋስትና ከተፈቀደላቸው በኋላ ከእስር ያለመፍታት አካሄዱን እንዲያቆምም አሳስቧል። አንዳንድ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች ጋዜጠኞችን ችግር ፈጣሪ አድርገው እያዩ ነው በማለትም ማኅበሩ ወቅሷል። ማኅበሩ በብሄራዊ ንግግር ኮሚሽኑ ሚና እንዲኖረው እንዲደረግም ጨምሮ ጠይቋል።

4፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 52 ብር ከ0734 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 53 ብር ከ1149 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 58 ብር ከ8257 ሳንቲም፣ መሸጫው 60 ብር ከ0022 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ52 ብር ከ1515 ሳንቲም ሲገዛ እና በ53 ብር ከ1945 ሳንቲም ሲሸጥ ውሏል። የአንድ ቻይና ዩዋን ደሞ በ6 ብር ከ9833 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ7 ብር ከ1230 ሳንቲም ተሽጧል።

5፤ የሱማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐመድ በኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ግብዣ ለሁለት ቀናት ኦፊሴላዊ ጉብኝት ዛሬ ኬንያ መግባታቸውን የፕሬዝዳንት ሞሐመድ ጽሕፈት ቤት በትዊተር ገጹ አስታውቋል። ፕሬዝዳንቱ በኬንያ ቆይታቸው፣ ከኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚወያዩ ተገልጧል። ሱማሊያ ላለፉት ሁለት ዓመታት በኬንያ የጫት ምርት ላይ የጣለችውን እገዳ ፕሬዝዳንት ሞሐመድ በቅርቡ ማንሳታቸው ይታወሳል።

6፤ የሱማሊያው ፕሬዝዳንት ሞሐመድ ኤርትራ ያሰለጠነቻቸው የሱማሊያ ምልምል ወታደሮች በቅርቡ ወደ አገራቸው እንደሚመለሱ ለሰልጣኞቹ ቤተሰቦች መናገራቸውን የፈረንሳዩ ዜና ወኪል ዘግቧል። ሥልጠናቸውን ካጠናቀቁ ዓመት ያለፋቸው ምልምሎቹ መቼ እንደሚመለሱ ግን ፕሬዝዳንቱ ቁርጥ ያለ ጊዜ አላስቀመጡም። ምልምሎቹ አምስት ሺህ የሚገመቱ ሲሆን፣ ፕሬዝዳንቱ በኤርትራ ጉብኝታቸው በትክክል ስንት ሰልጣኞች መኖራቸውን እንዳረጋገጡም አልገለጹም።

@Ethiopianewsagency (ኢዜአ)
170 viewsedited  18:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 08:47:18 የአማራ ባንክ መምጣት ሶስተኛውን የባንክ ኢንደስትሪ ማዕበል አፋፍሞታል

የአማራ ባንክ መቋቋምን ተከትሎ ከ1987 ዓ.ም ወዲህ የባንኩ ዘርፍ ሶስተኛውን ማዕበል እያስተናገደ ነው። የመጀመሪያው የ1987ቱን ህገ መንግስት ተከትሎ የግል ባንኮች መጀመርና መስፋፋት በዘርፉ አዳዲስ የውድድር መንፈስ ይዞ ብቅ ማለቱ ይታወሳል። ሁለተኛው የባንክ ዘርፉ አብይ ክስተት (ማዕበል) 2000 ዓም በኋላ የተቋቋሙና በስርጭትም ሰፋ ብለው የታዩት ባንኮች ይዘውት የመጡት ፉክክር ነው። ሶስተኛው የባንኮች ብርቱ የፉክክር ዘመን ባለፉት ሶስት ዓመታት ከወለድ ነፃ፣ ማይክሮ ፋይናንስና የቤቶች ባንኮች መስፋፋትን ተከትሎ የተጀመረው ነው።

22ኛ የኢትዮጵያ ባንክ ሆኖ ሰኔ 11 2014 ዓ.ም በይፋ ስራ የጀመረው አማራ ባንክ የኢትዮጵያን የባንክ ኢንዱስትሪ ውድድር ወደ አዲስ ምዕራፍ እየወሰደው መሆኑን የሚጠቁሙ መረጃዎች አሰባስበናል። ባንኩ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ የተቀላቀለበት 6.5 ቢልየን ብር ካፒታል በግሉ ዘርፍ ከተደረጉ የፋይናንስ ዘርፍ የጅማሮ ኢንቨስትመንት ቀዳሚ ያደርገዋል። 

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የበጀት አመቱ ሁለተኛ ሩብ አመት የሪፖርት መጽሄት እንደሚያሳየው የመንግስቶቹን ጨምሮ አጠቃላይ የኢትዮጵያ ባንኮች ካፒታል 167.1 ቢሊየን ብር መድረሱን ያሳይና ከዚህ ወስጥ 81 ቢሊየን ብር ካፒታሉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የልማት ባንክ ሆኖ ቀሪው 86 ቢሊየን ብር የግል ባንኮች መሆኑን ይጠቅሳል። አማራ ባንክ ከግል ባንኮቹ ጠቅላላ ከፒታል ስምንት በመቶውን ያክል ይዞ ነው ስራ የጀመረው። 

ብሄራዊ ባንክ እስከ ቅርብ  ጊዜ ሲጠቀምበት በነበረው ህግ የባንክ መመስረቻ ካፒታል 500 ሚልየን ብር ሲሆን ይህ የካፒታል መጠን ከዚህ በኋላ አዲስ ለሚመሰረት ባንክ ጥቅም ላይ እንደማይውልና በጥቂት አመታት ውስጥም ስራ ላይ ያሉ የግል ባንኮች ካፒታላቸውን ወደ 5 ቢሊየን ማሳደግ እንዳለባቸው ግዴታ ተቀምጦባቸዋል። 

እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ እንደተስተዋለው ብዙ በምስረታ ላይ የነበሩ ባንኮች የ500 ሚልዮን ብሩን መነሻ ካፒታል ማሟላት አቅቷቸው ምስረታቸው መክኖ ያውቃል።

የአማራ ባንክ የማርኬቲንግ እና ብራንዲንግ ዳይሬክተር አቶ አስቻለው ታምሩ እንደተናገሩት በ70 የባንክ ቅርንጫፎች ስራውን የጀመረው አማራ ባንክ እስከ ሰኔ 30 2014 አ.ም ባቀደው መሰረት 100 ቅርንጫፎችን ከፍቷል። ብዙ የግል ባንኮች 100 ቅርንጫፍ ለመድረስ ቢያንስ አመት ወስዶባቸዋል። 

“በዘርፉ ላይ መነቃቃትን እየፈጠርን እንደሆነ እናስባለን ይህም የተለያዩ ባንኮች እየወሰዱት ባለው እርምጃ ሊታይ ይችላል።” ብለውናል አቶ አስቻለው ። 

ያደረግነው የዘርፉ ቅኝት እንደሚያሳየውም የአማራ ባንክ መመስረቱን ተከትሎ የንግድ ባንኮች ከሰራተኛ ደሞዝ ከማስተካከልና ጥቅማ ጥቅም ከመስጠት ጀምሮ አዳዲስ ፈተናውን የመቋቋሚያ መላ እየቀየሱ ነው። 

መንግስታዊው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አንስቶ ነባር የብድር ባለሙያዎችን ጨምሮ በርካታ ሰራተኞች ለቀው አማራ ባንክን እንደተቀላቀሉ መረዳት ችለናል። 

@Ethiopianewsagency (ኢዜአ)
172 viewsedited  05:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ