Get Mystery Box with random crypto!

የ2012 የትምህርት ዘመን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ቀናት #የተረጋገጠ ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርሲቲዎች የ | Ethiopian Students

የ2012 የትምህርት ዘመን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ቀናት #የተረጋገጠ
ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርሲቲዎች የሚያመሩ ተማሪዎች
I. የትምህርት ማስረጃዎቻቸውን ዋናውን እና ሁለት ኮፒዎች፣
• የ8ኛ ክፍል (ሚኒስትሪ) ሰርተፊኬት
• የ10ኛ እና የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ሰርተፊኬቶች
• ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የተማራችሁበትን ትራንስክሪፕት
II. 8 ፓስፖርት ሳይዝ ፎቶ ግራፍ (የቅርብ ጊዜ)
III. አንሶላ እና ብርድ ልብስ
IV. የስፖርት አልባሳት (ጫማን ጨምሮ)
** ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲዎች የሚኖራቸውን ቆይታ ሰላማዊ ለማድረግ የተማሪ ወላጆች ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር የዋስትና ውል እንዲገቡ መደረጉ ይታወቃል።

ስለዚህ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲዎቹ በሚሄዱበት ወቅት ወላጆቻቸው የተፈራረሙበትን ሰነድ ይዘው እንዲገኙ ዩኒቨርሲቲዎቹ ጠይቀዋል። ተማሪዎቹ ሰነዶቹን ከየሚኖሩበት ወረዳ መውሰድ ይችላሉ።

ተጨማሪ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን ሲጠሩ ተከታትለን የምናሳውቃችሁ ሲሆን ከታች የተዘረዘሩት ቀናት ላይ የጊዜ ለውጥ ካለም ለውጡን የምናሳውቃችሁ ይሆናል።

Via:- EBC
@YeneTube @Fikerassefa