Get Mystery Box with random crypto!

የነሐሴ ፲፪ ግጻዌ ❖ ምስባክ ዘነግህ በቅድመ መላእክቲከ እዜምር ለከ፣ ወእሰግድ ውስተ ጽርሐ መቅ | የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

የነሐሴ ፲፪ ግጻዌ

❖ ምስባክ ዘነግህ
በቅድመ መላእክቲከ እዜምር ለከ፣
ወእሰግድ ውስተ ጽርሐ መቅደስከ።
ወእገኒ ለስምከ፤
ትርጉም፦
በመላእክት ፊት እዘምርልሃለሁ።
ወደ ቅዱስ መቅደስህ እሰግዳለሁ፤
ስምህንም አመሰግናለሁ።
( መዝ ፻፴፯ : ፩-፪ )

❖ ወንጌል ዘነግህ
ማቴዎስ ፳፭ : ፴፩-ፍጻሜ /25:31-ፍጻሜ

መልእክታት:-
➊. ፩ኛ ቆሮንቶስ ፱ : ፲፯ - ፍጻሜ /9:17-ፍጻሜ
➋. ይሁዳ ፩ : ፰ - ፲፬ /1:8-14
➌. የሐዋ/ሥራ ፳፬ : ፩ - ፳፪ /24:1-22

+ ምስባክ ዘቅዳሴ
እግዚኦ ኲነኔከ ሀቦ ለንጉሥ።
ጽድቀከኒ ለወልደ ንጉሥ።
ከመ ይኰንኖሙ ለሕዝብከ በጽድቅ።
ትርጉም፦
አቤቱ፥ ፍርድህን ለንጉሥ ስጥ፥
ጽድቅህንም ለንጉሥ ልጅ፥
ሕዝብህን በእውነት ይዳኝ ዘንድ።
(መዝ ፸፩ : ፩ /71:1)

+ ወንጌል ዘቅዳሴ
የማቴዎስ ወንጌል ፳፪ : ፩ - ፲፭ /22:1-15
"፩
ኢየሱስም መለሰ ደግሞም በምሳሌ ነገራቸው እንዲህም አለ።

መንግሥተ ሰማያት ለልጁ ሰርግ ያደረገ ንጉሥን ትመስላለች።

የታደሙትንም ወደ ሰርጉ ይጠሩ ዘንድ ባሮቹን ላከ ሊመጡም አልወደዱም።

ደግሞ ሌሎችን ባሮች ልኮ። የታደሙትን። እነሆ፥ ድግሴን አዘጋጀሁ፥ ኮርማዎቼና የሰቡት ከብቶቼ ታርደዋል፥ ሁሉም ተዘጋጅቶአል፤ ወደ ሰርጉ ኑ በሉአቸው አለ።

እነርሱ ግን ቸል ብለው አንዱ ወደ እርሻው፥ ሌላውም ወደ ንግዱ ሄደ፤

የቀሩትም ባሮቹን ይዘው አንገላቱአቸው ገደሉአቸውም።

ንጉሡም ተቈጣ፥ ጭፍሮቹንም ልኮ እነዚያን ገዳዮች አጠፋ፤ ከተማቸውንም አቃጠለ።

በዚያን ጊዜ ባሮቹን። ሰርጉስ ተዘጋጅቶአል፥ ነገር ግን የታደሙት የማይገባቸው ሆኑ፤
.
.
፲፬
የተጠሩ ብዙዎች፥ የተመረጡ ግን ጥቂቶች ናቸውና።"

+ ቅዳሴ - ዘእግዝእትነ ወይም ዘዮሐንስ አፈወርቅ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox