Get Mystery Box with random crypto!

'አራት ፖሊሶች እጆቼን ይዘው በምላጭ ያንገቴን ማህተም በጠሱት' በሕይወቴ ጥቁር ጠባሳ የጣለብኝ | 💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

"አራት ፖሊሶች እጆቼን ይዘው በምላጭ ያንገቴን ማህተም በጠሱት"

በሕይወቴ ጥቁር ጠባሳ የጣለብኝ እስር !!

ከታሰርኩባቸው እስሮች ትንሹ የሚባለው ይሄኛው እስር ቢሆንም ከፍተኛ ግፍና ማስጠንቀቂያ ያዘለ እስር ነው ፤ ዝርዝሩን በሰፊው እመለስበታለሁ ። ከመጀመሪያ ጀምሮ ማህተቤን እንድበጥስ ግፊት ቢደረግብኝም ያንን ማደረግ እንደማልችል እና ለእኔ ሞት እንደሆነ ነግሬ አልበጥስም አልኩ !! ከአንድ ቀን ጭቅጭቅ በኋላ አራት ፖሊሶች ብቻዬን በማስጠራት ሳላስበው እጆቼን ከያዙ በኋላ
በምላጭ ያንገቴን ማህተብ በጠሱት እቅም የማጣት ስሜት ተሰማኝ ፤ እንዲደበድብኝ ተሳደብኩ እነሱ ከዱላ በላይ የሆነ ነገር እንዳደረሱብኝ ስለገባቸው ዝም አሉኝ ።

መብላት መጠጣት አቃተኝ በአይኤስ አይኤስ በሰው ሀገር ማህተባችንን አልበጥስም ብለው የተሰው ወንድሞቼ አይነት አቅም እንደሌለኝ ሲሰማኝ ልቤ ክፉኛ ተሰበረ ፤ኡፍፍ ይህ ክፉ ቀን መቼም አረሳወም !!

ይህ እንዲህ እንዳለ ፤ሁሌም ከግፉዓን ጎን የሚቆመው ወንድማችን ጠበቃ ቤተማርያም አለማየሁ በዚህ ፈተና ወቅት ሙያዊ ግዴታው እንዳለ ሆኖ! እንደወትሮ አሁንም ፤ስለ ፍትህ ፤ስለ እውነት በማለት ከእኔ በደለኛ ጎን በመቆም ወንድሜ ቤተ እግዚአብሔር እድሜና ጤና ይስጥህ ፤ አመሰግናለሁ ።

ሁሌም ቢሆን የግፉአን ዓይንና ጆሮ በመሆን የበደለኞችን ድምጽ የምታሰሙ ፤ጋዜጠኞች ፤አክቲቪስቶች ክብር ለእናንተ ይሁን !!

ብቻ ፈተውኛል ለሁላቹም እግዚአብሔር ይስጥልኝ !!