Get Mystery Box with random crypto!

#NewsAlert በቤኒሻንጉል ጉመዝ ክልል ውስጥ 'የከፋ' የአመራር ችግር የታየባቸው አመራሮች ከ | ESAT International

#NewsAlert

በቤኒሻንጉል ጉመዝ ክልል ውስጥ 'የከፋ' የአመራር ችግር የታየባቸው አመራሮች ከኃላፊነት ሲነሱ የከፋ አመራር የለባቸውም የተባሉት ደግሞ ሽግሽግ አደረጉ !

የቤንሻንጉል ጉሙዝ ብልፅግና ፓርቲ ፥ በቅርቡ የተካሄደውን የከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ኮንፈረንስ ተከትሎ ህብረ-ብሔራዊነትን በጠበቀ መልኩ አዲስ የአመራር ምደባ እና ሽግሽግ መደረጉን አሳወቀ።

በህዝብ በማስተቸት የከፋ ችግር የታባታቸውን አመራሮች በማንሳት በአዲስ እንዲተኩ በማድረግና የከፋ ችግር የሌለባቸውን ደግሞ በማሸጋሸግ የመተከል ዞንና ወረዳዎች መዋቅር መልሶ የማደራጀት ስራ ተሰርቷል ብሏል።

የመተከል ዞን መምሪያ መዋቅር መልሶ ለማደራጀት በተወሰደ እርምጃ የትምህርት መምሪያ ፣ የከተማ ልማት እና የንግድ መምሪያ፣ ግብርና ተፈጥሮ ሀብት መምሪያ፣ ፍትህ መምሪያ እንዲሁም የውሃ እና ማዕድን መምሪያ ኃላፊ ቦታ ላይ የአመራር አዲስ ምደባና ሽግሽግ ስራ ተሰርቷል ተብሏል።

- የወምበራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ እና ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ቦታዎች በሌላ አመራር እንዲተኩ ተደርጓል።

- የቡለን ወረዳ ምክትል ዋና አስተዳዳሪ እና ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ቦታዎች በሌላ አመራር እንዲተኩ ተደርጓል።

- የድባጢ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ቦታ በሌላ አመራር እንዲተካ ተደርጓል።

- የማንዱራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ቦታ በሌላ አመራር እንዲተካ ተደርጓል።

- የጉባ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ እና ምክትል ዋና አስተዳዳሪ ቦታዎች በሌላ አመራር እንዲተኩ ተደርጓል።

በተመሳሳይ የካቢኔ እና የጽ/ቤት ኃላፊ ቦታዎች ላይ የአመራር አዲስ ምደባ እና የማሸጋሸግ ስራ በመስራት መልሶ የማዋቀር ስራ መስራቱ ተገልጿል።

* ዝርዝር መግለጫው ከላይ ተያይዟል።

@ethiomereja1 ሼር