Get Mystery Box with random crypto!

🇪🇹ኢትዮ-News መረጃ

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiomereja0 — 🇪🇹ኢትዮ-News መረጃ
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiomereja0 — 🇪🇹ኢትዮ-News መረጃ
የሰርጥ አድራሻ: @ethiomereja0
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 9.06K
የሰርጥ መግለጫ

Broadcast & media production company
⌛️ አለም አቀፋዊነት 🌐 🌐 🌐
⌛️ ወቅታዊነት ⌚️🕰🎙
⌛️ ተደራሽነት 📲💻📡📺
⌛️ ሚዛናዊነት ⚖ ⚖ ⚖
ከኛ ጋር ይሁኑ | ያጋሩ
https://t.me/ethiomereja0
https://t.me/ethiomereja0

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-10-26 01:42:24 #AU

የኢትዮጵያ መንግስት እና የህወሓትን የሰላም ንግግር በተመለከተ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፋኪ ማህማት መግለጫ አውጥተዋል።

በመግለጫው ምን አሉ ?

- የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት #ለመጀመሪያ ጊዜ ፊት ለፊት የተገናኙበት የሰላም ንግግር ዛሬ በደቡብ አፍሪካ ተጀምሯል።

- በሰላም ንግግሩ ላይ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ድርጅት (IGAD)
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ፣ የአሜሪካ መንግስት ተወካዮች በታዛቢነት እየተሳተፉ ነው።

- ደቡብ አፍሪካ የሰላም ንግግሩን ለማስተናገድ ፍቃደኛ ስለሆነች ለሀገሪቱ መንግስት እና ለፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፖሳ ምስጋና አቅርበዋል።

- ሙሳ ፋኪ ማሀመት የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት የኢትዮጵያን ጥቅም ባስጠበቀ ሁኔታ ሰላምን ለማስፈን እና ለግጭቱ ዘላቂ ፖለቲካዊ መፍትሄ እንዲገኝ ለማስረግ ባሳዩት ቁርጠኝነት ይበልጥ እንደተበረታቱ ገልፀዋል።

- የአፍሪካ ህብረት " የሰላም ንግግር " ተሳታፊ ወገኖች ኢትዮጵያ፤ በኢትዮጵያውያን ባለቤትነት እና በአፍሪካ ህብረት መሪነት ሰላም እንዲሰፍን ፣ የተረጋጋችና አንድነቷ የተጠበቀ እንድትሆን ህብረቱ ድጋፉን እንደሚቀጥል ቁርጠኛ መሆኑን ገልፀዋል።

https://t.me/ethiomereja0
1.7K views22:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 20:58:46 «የብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር ይናገር ደሴ

- ኢትዮጵያዊያን በግለሰብ ደረጃ ከ100 ሺህ ብር በላይ ለድርጅቶች ደግሞ ከ200 ሺህ ብር በላይ ቤት ውስጥ ማስቀመጥ የተከለከለ መሆኑን መገንዘብ ይኖርባቸወል።

- ገንዘብ በባንክ መቀመጥ አለበት ፤ የግብይት ስርዓትም በባንክ ማካሄድ ይቻላል።

- መመሪያው ከሚፈቅደው የገንዘብ መጠን በላይ አስቀምጦ የተገኘን አካል #የጠቆመ ግለሰብ 15 በመቶ የወረታ ክፍያ ይከፈለዋል።

- በውጭ አገራት ገንዘብ ግብይት መፈጸምም ሆነ በህገወጥ መንገድ ይዞ መገኘት አይቻልም።

- ወርቅን በህገወጥ መልኩ ቤት ውስጥ ማከማቸት የማይቻል ሲሆን በህገወጥ መልኩ ወርቅን ያከማቸ ግለሰብ ለጠቆመ ግለሰብ ባንኩ በወቅቱ ባለው ግብይት የ15 በመቶ ወረታ ይከፈለዋል።

- በህገወጥ የሃዋላ የውጭ አገራት የተሰማሩ አካላትን ለጠቆመም እስከ 25 ሺህ ብር ወረታ ይከፈለዋል።

- በህገወጥ ገንዘብ ህትመት የተሰማሩ አካላትን ያጋለጠም ከ20 ሺህ እስከ 200 ሺህ ብር ወረታ ይከፈለዋል።

- ጠቋሚዎች ወረታውና ሽልማቱ የሚበረከትላቸው #ደህንነታቸው እና #ሚስጥራዊነታቸው በተጠበቀ መልኩ ነው።

Credit : ENA»


https://t.me/ethiomereja0
305 views17:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-02 15:28:16 አሜሪካ ሱዳንን አስጠነቀቀች።

በሱዳን የአሜሪካ አምባሳደር ጆን ጎድፍሬይ ፤ ካርቱም ሩሲያ በቀይ ባህር ዳርቻ የጦር ሰፈር እንድትመሰርት ከፈቀደች ከባድ መዘዝ እንደሚኖረው አስጠንቅቀዋል።

ከ25 ዓመታት በኋላ በሱዳን የመጀመርያው የአሜሪካ አምባሳደር የሆኑት ጎድፍሬይ እንዲህ ዓይነት ውሳኔ ሱዳንን ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ መነጠል ብቻ ሳይሆን ጥቅሟን የሚጎዳ ነው ሲሉ አስገንዝበዋል።

አምባሳደር ጎድፍሬይ ከሱዳን አል ታይያር ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ፤ "ሩሲያ በቀይ ባህር ላይ የጦር ሰፈር ለመመስረት እ.ኤ.አ. በ2017 ከስልጣን ከተወገዱት ፕሬዝዳንት ኦማር አልበሽር ጋር የተፈራረመችውን ስምምነት ተግባራዊ ለማድረግ እየሞከረች ነው የሚሉ አንዳንድ ሪፖርቶች አሉ"  ብለዋል።

አልበሽር ለወራት የዘለቀን ተቃውሞ ተከትሎ ከስልጣን የተወገዱት በሚያዝያ 2019 እንደነበር ይታወቃል።

የአሜሪካው ዲፕሎማት " የሱዳን መንግስት የጦር ሰፈሩ (የሩስያ) እንዲቋቋም እንዲቀጥል ከወሰነ ወይም እንደገና ለመደራደር ከወሰነ ለሱዳን ጥቅም ጎጂ ነው " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

" ሁሉም አገሮች ከየትኞቹ አገሮች ጋር አጋር እንደሚሆኑ የመወሰን ሉዓላዊ መብት አላቸው " ያሉት አምባሳደሩ " ነገር ግን እነዚህ ምርጫዎች በእርግጥም መዘዝ አላቸው " ሲሉ አፅንዖት ሰጥተዋል።

እንደ ዲፕሎማቱ ገለጻ አሜሪካ በሱዳን አዲስ በሲቪል የሚመራ መንግስት እና ሀገሪቱን ወደ ዲሞክራሲያዊ ጎዳና የሚመልስ የሽግግር ማእቀፍ ለማየት ትፈልጋለች።

እ.ኤ.አ ህዳር 2017 ሱዳን እና ሩሲያ በወታደራዊ ስልጠና፣ የልምድ ልውውጥ እና የጦር መርከቦችን ወደ ሁለቱ ሀገራት ወደቦች ለማስገባት የትብብር ስምምነቶችን ተፈራርመዋል።

ያንብቡ : telegra.ph/Sudan-Tribune-09-29

ምንጭ፦ ሱዳን ትሪቢዩን

https://t.me/ethiomereja0
627 views12:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-02 14:02:02 #ጋምቤላ

የጋምቤላ ክልል መንግስት የኢሰመኮን ሪፖርት "ለጠላት የወገነ ነው " ሲል ገልጾ ሪፖርቱን እንደማይቀበለውና እንደሚያወግዘው ገለፀ።

የጋምቤላ ክልል፤ "ኢሰመኮ ሰኔ 7/2014 ዓ.ም በጋምቤላ ክልል ጋምቤላ ከተማ ላይ ተፈጥሮ በነበረው ውጊያ ተከትሎ በክልሉ ልዩ ኃይሎች፣ ሚሊሽያ እና ተባባሪ ወጣቶችን ሲመሩ የነበሩ አመራሮች አማካይነት ደረሰ ባላቸው የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ላይ ያወጣውን ሚዛናዊነት የጎደለውና የአንድ ክልል የፀጥታ ተቋምን ከተራ የአሸባሪ ቡድን ተላላኪ ጋር በአንድነት ያየ" ነው ሲል ገልጿል።

ሪፖርቱ "ከሁሉ በላይ በክልልና በአገር ላይ ይደርስ የነበረ ከፍተኛ ጥቃት በመቀልበስ ሂደት የህይወት መስዋዕትነት የከፈለውን የፀጥታ ተቋማችንን በጅምላ የፈረጀና የተገኘውንም ድል በዜሮ ያባዛ ሆኖ አግኝቶታል" ብሏል።

በዚህም የጋምቤላ ክልል መንግሥት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የምርመራ ሪፖርት እንደማይቀበለውና አጥብቆ እንደሚያወግዘው ገልጿል።

አክሎም "የክልሉ መንግሥት ምንም እንኳን አንድም የዜጋ ህይወት እንዲጠፋ የሚፈቅድ ባይሆንም በጥፋት ቡድኖቹ በተከፈተብን ጥቃት ከንፁሃን ዜጎች እንዲሁም የፀጥታ አካላት ህይወት መጥፋት ጋር ተያይዞ ኮምሽኑ ያወጣው የምርመራ ሪፖርት ግኝት እጅግ የተጋነነ እና በወቅቱ መሬት የነበረውን ጥሬ ሀቅ ያላገናዘበ" ነው ብሏል።

"የኢትዮጵያ ህዝቦች በጋምቤላ ከተማ ውስጥና ኦነግ ሸኔና ጋነግ የፈፀሙት ወረራና ጥቃት ብዥታ ተፈጥሮ የክልሉን መንግሥት እና ህዝብ በወቅቱ የተደረገውን ተጋድሎና ለዚህም የተከፈለውን መስዋዕትነት በዜሮ ያባዛ፤ ከሁሉ በላይ የክልሉን የፀጥታ ኃይል ሞራል የሚያዳክም፤ ፀረ-ሠላም ኃይሉንና መንግሥትን በአንድ ሚዛን ላይ አድርጎ ያየ በአጠቃላይ ለጠላት የወገነ ሪፖርት ሆኖ አግኝተነዋል" ሲል አሳውቋል።
https://t.me/ethiomereja0
713 views11:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-28 11:50:19 #EHRC

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጳጉሜ 1 ቀን 2014 ዓ.ም. በኦሮሚያ ክልል፣ ሆሮጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ በሲቪል ሰዎች ላይ የደረሰን ግድያ አስመልከቶ ባወጣው መግለጫ በዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች ተጨማሪ የጸጥታ ሥጋቶች በመኖራቸው በታጠቁ ቡድኖች በሲቪል ሰዎች ላይ ብሔርን መሰረት ያደረጉ ተጨማሪ ጥቃቶች እንዳይፈጸሙ ለመከላከል በትኩረት እንዲሠራ ማሳሰቡን ይታወሳል።

ኢሰመኮ በአካባቢው ሲቪል ሰዎችን ኢላማ ያደረጉ ጥቃቶች አሁንም ተሰፋፍተው መቀጠላቸው ገልጾ እጅግ አሳሳቢ መሆኑን አስገንዝቧል።

በዞኑ በአሙሩ፣ በሆሮ ቡልቅ እና በጃርደጋ ጃርቴ ወረዳዎች ከነሐሴ 25 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ባሉት ሦስት ሳምንታት ውስጥ ብቻ በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (በተለምዶ ኦነግ ሽኔ)፣ በአማራ ኢመደበኛ ታጣቂ ኃይሎች እና ግለሰቦች በተከታታይ በተፈጸሙ ጥቃቶች ከ100 በላይ ሲቪል ሰዎች የተገደሉ መሆኑ ታወቋል ሲል ኢስመኮ ገልጿል።

እንዲሁም የግል ንበረት እና የቁም ከብቶች መዘረፋቸውን ፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎችም ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ያለበቂ የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ የሚገኙ መሆኑን ኮሚሽኑ ከተጎጂ ቤተሰቦች፣ ከአካባቢው የፍትሕና የአስተዳደር አካላት እንዲሁም በአካባቢው ከሚንቀሳቀሱ የእርዳታ ድርጅቶች ያሰባሰብኳቸው መረጃዎች እና ማስረጃዎች ያሳያሉ ብሏል።

የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ " የክልሉ አና የፌዴራል መንግሥታት በአካባቢው ብሔርን መሰረት አድርገው የሚፈጸመው ጥቃቶችን ለመከላከል በመወሰድ ላይ የሚገኙትን እርምጃ ችግሩን በሚመጥን ደረጃ በማሳደግ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ሊወጡ ይገባል" ሲሉ በድጋሚ አሳስበዋል።

https://t.me/ethiomereja0
742 views08:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-19 00:39:43 #EthioTelecom

ኢትዮ ቴሌኮም የ " ኢ-ሲም " አገልግሎት መጀመሩን ገልጿል።

" ኢ-ሲም " በቀላሉ ከስልክ ቀፎ ጋር በማናበብ ብቻ የሞባይል ስልክ አገልግሎት ማግኘት የሚያስችል አዲስ ቴክኖሎጂ ሲሆን ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ ፤ " ቸርችል ጎዳና " በሚገኘው የፕሪሚየም አገልግሎት ማዕከሉ ማግኘት እንደሚቻል አሳውቋል።

በቅርቡ ፤ በሁሉም የአገልግሎት መስጫ ማዕከሎቹ አገልግሎቱን መስጠት እንደሚጀምር ገልጿል።

የኢ-ሲም አገልግሎት የሚሰጣቸው ጥቅሞች ምንድናቸው ?

- ቀላል እና ብቁ የኔትወርክ ግንኙነት፤

- በአንድ ስልክ ከአንድ በላይ የአገልግሎት ቁጥር መጠቀም የሚያስችል፤

- ሲም ካርድ እየቀያየሩ መጠቀምን ያስቀራል፤

- ላፕቶፕ ፣ ስማርት ሰዓት ፣ ታብሌት የመሳሰሉትን በቀላሉ ለማገናኘት ፣ ለአምራቾች፣ አከፋፋዮች እና አገልግሎት ሰጪዎች፣ ለትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች እንዲሁም የተለያዩ ዲጂታል ዲቫይሶችን በቀላሉ በማገናኘት ቀልጣፋ አገልግሎት የማግኘት ፍላጎት ላላቸው ሁሉ የቀረበ መሆኑን ኢትዮ ቴላኮም ገልጿል።

በኢ-ሲም የሚሰሩ ስልኮች የትኞቹ ናቸው ?

#Samsung

Samsung Galaxy S20
Samsung Galaxy S20+
Samsung Galaxy S20 Ultra
Samsung Galaxy S21
Samsung Galaxy S21+ 5G
Samsung Galaxy S21+ Ultra 5G
Samsung Galaxy S22
Samsung Galaxy S22+
Samsung Galaxy Note 20
Samsung Galaxy Note 20 Ultra 5G 
Samsung Galaxy Fold
Samsung Galaxy Z Fold2 5G
Samsung Galaxy Z Fold3 5G
Samsung Galaxy Z Flip

#iPhone

iPhone XR
iPhone XS
iPhone XS Max
iPhone 11
iPhone 11 Pro
iPhone SE 2 (2020)
iPhone 12
iPhone 12 Mini
iPhone 12 Pro
iPhone 12 Pro Max
iPhone 13
iPhone 13 Mini
iPhone 13 Pro
iPhone 13 Pro Max
iPhone SE 3 (2022)

#Google

Google Pixel 3a XL
Google Pixel 4
Google Pixel 4a
Google Pixel 4 XL
Google Pixel 5
Google Pixel 5a
Google Pixel 6
Google Pixel 6 Pro.
Google Pixel 3 XL
Google Pixel 2 XL

#Huawei

Huawei P40
Huawei P40 Pro
Huawei Mate 40 Pro

#Motorola

Motorola Razr 2019
Nuu Mobile X5
Gemini PDA
Rakuten Mini

#Oppo

Oppo Find X3 Pro
Oppo Reno 5A
Oppo Reno6 Pro 5G

#eSIM #DigitalSIM #EthioTelecom

https://t.me/ethiomereja0
1.3K views21:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-17 20:39:05 "ህይዎት በፈረቃ ናትና ታገስ "

ምድራዊ ህይዎት ተፈጥሮዋ ፈረቃ ነው።ፍፁም ተድላና ፍፁም ችጋር የሚባል ነገር የለም።

ደስታና ሀዘን፣ረሃብና ጥጋብ፣ህይዎትና ሞት፣ብርሃንና ፅልመት፣ትዳርና ፍቺ፣ጤና እና ህመም፣ልፋትና እረፍት፣ጦርነትና ሰላም፣ትርፍና ኪሳራ፣ክረምትና በጋ፣መውደቅና መነሳት፣ዕውቀትና ድድብና፣ሁከትና ፀጥታ፣ችኮላና እርጋታ፣..........የዚች አለም የፈረቃ ገፆች ናቸው።

ትናንት ድሃ የነበሩ አገሮች ዛሬ በሃብታቸው አለምን እየገዙት ነው።ተሰብረው የነበሩት ተጠግነው መራመድ ችለዋል።የተጣሉት ታርቀው ወዳጅ ሆነዋል።የተናቁ የነበሩት ዛሬ አለም እየሰገደላቸው ነው።መካኖች ልጅ ወልደው ስመዋል፣ሃያላን ተሰባብረው ጎዳና ላይ ወድቀዋል፣.............

ዋናው ነገር ሁለቱንም ፈረቃዎች በትዕግስትና በጥበብ ማስተናገድ ነው።የክረምቱ ወጀብ ተገልጦ የበጋው ፀሃይ እንደሚበሰረው ሁሉ ዛሬ ያለንበት የችግር ዶፍ አባርቶ የብልፅግናችንን ፀደይ የምናይበት ጊዜ ሩቅ አይደለም።

ዛሬ ላይ ጠላት ቢበዛም ነገ መበተኑ አይቀሬ ነው።የዛሬው መጥፎ ገጠመኝ ለነገው ብሩህ ተስፉ ቦታውን ለቆ መሄዱ የጊዜ ጉዳይ እንጂ ግደታ ነው።ዛሬ በጥጋብ የፈነጩብን ነገ እንደማያፍሩ ዋስትና የላቸውም።

የዛሬ መከረኛ ሌሊቶች በነገ የማለዳ ጮራዎች ተገፈው ያነቡ አይኖች ይታበሳሉ።ያስቸገሩን ኮረብታዎች ሁሉ በተባበረ ክንዳችን ይደረመሳሉ።የወጋን ቡዳ ማርከሻውን ሲያገኝ ይረክሳል።ሊፈጀን ያሰፈሰፈው ባቀጣጠለው እሳቱ ተቃጥሎ አመድ ሆኖ ይበናል።

ሰውና ትዕግስት አብሮ አደግ ናቸው።ከስልጣን ያወረዱትን፣ከማህበራዊ መስተጋብሩ ያገቱትን፣በኢኮኖሚ ማዕቀብ አሳምመው የቀጡትን፣በቀዬው ባይታወር ያደረጉትን ሁሉ በትዕግስት ትቷቸው እያለፈ ዛሬ ላይ ደርሷል።


ዛሬና ትናንት ፍፁም አንድ አይደሉም።ፀንፈኝነት፣አግላይነት፣ደሴትነቴ፣ከፋፋይነት፣ስግብግብነት፣በኪነት መግዘፍ፣ቤት ዘግቶ መብላት፣ወዘተ የፍፃሜ ጊዚያቸውን ሊያገኙ የመጨረሻው ትራክ ላይ ደርሰናል።የሚጠበቅብን ሁነቶችን በትዕግስት፣በጥበብና በስራ አጅቦ ማስተናገድ ብቻ ነው።"ቀን አለና ቀና ብለህ ተራመድ "እንዲሉ በዛሬው የችግር ናዳ አንገትህን ደፍተህ ከመራመድ ይልቅ የነገውን የተስፋ ጮራ እያማተርክ ቀና ብለህ ተራመድ።

እናም አብሽሩ!ሁሉም ለበጎ ነው!እርጎ ካልተገፋ ቂቤ አይወጣውም።እንጨት ካልጨሰ አይነዲም።ሻይ ካልተማሰለ ጣዕሙ አይታወቅም።በእርግጥም ከችግር በኋላ ድሎት አለና አይዞን!ነገ የእኛ አንገት ቀጥ ብሎ የግፈኞች አንገት መሰበሩ አይቀሬ ነው።


https://t.me/ethiomereja0
1.8K viewsedited  17:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 20:07:18 መረጃዎች በፍጥነት ለሁሉም እንዲደርሱ ሊንኩ ሼር ማድረግን አይርሱ!

https://t.me/ethiomereja0
1.5K views17:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 20:05:54 ሰበር ዜና

አሸባሪው ህውኀት ቆቦ ከተማን ተቆጣጠረ!
1.4K views17:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-13 06:54:26
የሰው ልጅ ይህን ያክል ጭካኔ ጫፍ ላይ የደረሰበት አሳዛኝ ቪድዮ ነው!

ይህ የምታዩት ወንድም ወንድሙን የሚደግልበት ቪድዮ ያሳዝናል! እንደዚህ አይነት ስራ እየተሰራ እንዴት ነው ታዲያ አምላክ ሊያዝንልን የሚችል!
8.9K views03:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ