Get Mystery Box with random crypto!

Ethio Home Solutions

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiohomesolutions — Ethio Home Solutions E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiohomesolutions — Ethio Home Solutions
የሰርጥ አድራሻ: @ethiohomesolutions
ምድቦች: ኢኮኖሚክስ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.43K
የሰርጥ መግለጫ

አድራሻ፡ መገናኛ ደራርቱ ሕንፃ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 226
ሥልክ፡ 0911248597 / 0940599595

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-07-16 07:12:36
የሚሸጥ ቦታ አዲስ አበባ ፣ጉርድ ሾላ
**************** ********
የሚገኝበት ቦታ፡ አዲስ አበባ፣ጉርድ ሾላ
ሥፋት 465 ካሬ ሜትር
ለቢሮ የተከራየ ቤት ያለበት
ዋጋ: 30 ሚሊዮን
************************
ለማንኛውም የቤት/ሕንፃ ግዥና ሽያጭ መረጃዎች ይፃፉልን/ይደውሉልን፡፡
ሥልክ፡ 0985055053
0918040000
ቴሌግራም፡ https://t.me/abaysalesagent
ኢሜል፡ abayengineeringpm@gmail.com
*************************
ያሉንን የቤት፣ሕንፃና መጋዘን ሽያጭ/ግዥ/ኪራይ መረጃዎችን ለማግኘት የቴሌግራምና የፌስቡክ ገፆቻችንን ይከታተሉ!
https://t.me/ethiohomesolutions
https://www.facebook.com/ethiohomesolutions
አድራሻችን፡ መገናኛ ደራርቱ ሕንፃ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 226
5.5K views04:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-16 07:09:35
የሚሸጥ ቦታ አዲስ አበባ ፣ቦሌ አራብሳ
**************** ********
የሚገኝበት ቦታ፡ አዲስ አበባ፣ቦሌ አራብሣ
ሥፋት 250 ካሬ ሜትር
ዋጋ: 7,000,000
************************
ለማንኛውም የቤት/ሕንፃ ግዥና ሽያጭ መረጃዎች ይፃፉልን/ይደውሉልን፡፡
ሥልክ፡ 0985055053
0918040000
ቴሌግራም፡ https://t.me/abaysalesagent
ኢሜል፡ abayengineeringpm@gmail.com
*************************
ያሉንን የቤት፣ሕንፃና መጋዘን ሽያጭ/ግዥ/ኪራይ መረጃዎችን ለማግኘት የቴሌግራምና የፌስቡክ ገፆቻችንን ይከታተሉ!
https://t.me/ethiohomesolutions
https://www.facebook.com/ethiohomesolutions
አድራሻችን፡ መገናኛ ደራርቱ ሕንፃ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 226
2.5K views04:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-16 07:06:21
የሚሸጥ ቤት አዲስ አበባ ፣አየር ጤና
**************** ********
የሚገኝበት ቦታ፡ አዲስ አበባ፣አየር ጤና
ሥፋት በይዞታ 460 ካሬ ሜትር
40 ሜትር አሥፓልት የያዘ
ዋጋ: 15,000,000
************************
ለማንኛውም የቤት/ሕንፃ ግዥና ሽያጭ መረጃዎች ይፃፉልን/ይደውሉልን፡፡
ሥልክ፡ 0985055053
0918040000
ቴሌግራም፡ https://t.me/abaysalesagent
ኢሜል፡ abayengineeringpm@gmail.com
*************************
ያሉንን የቤት፣ሕንፃና መጋዘን ሽያጭ/ግዥ/ኪራይ መረጃዎችን ለማግኘት የቴሌግራምና የፌስቡክ ገፆቻችንን ይከታተሉ!
https://t.me/ethiohomesolutions
https://www.facebook.com/ethiohomesolutions
አድራሻችን፡ መገናኛ ደራርቱ ሕንፃ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 226
5.2K views04:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 17:23:21
2.6K views14:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 22:47:50 ሀምሌ 01/ 2014 የወጣውን የ 20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ይመለከታል::

በከተማችን አዲስ አበባ ከሚስተዋሉ ችግሮች መካከል አንዱ የቤት አቅርቦት እጥረት ሲሆን ይህንኑ ደረጃ በደረጃ ለማቃለል አስተዳደሩ የተለያዩ አማራጮችን ነድፎ ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡

የዚህ ሂደት አካል የሆነው የነባሩ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ያሉበትን ወስብስብ ችግር ለይቶ በመፍታት ተመዝጋቢዎችን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ እና የቤት እጥረት ጫና ለመቀነስ የተደረገው ሰፊ ጥረት ተጠቃሽ ነው፡፡
በዚህ ሂደት በግንባታ ላይ የነበሩ 20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች መካከል 25,491 ያህሉ በቅርቡ ለባለ እድለኞች የዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት መካሄዱ ይታወቃል፡፡

ይህ የቤት ማሰስተላለፍ ስራ እንደ ከዚህ በፊቱ በቆጣቢወች መካከል አድሎና ብልሹ አሰራር እንዳይኖር ለማድረግ ግልፅነት በሚያሰፍን አግባብ ለማስተላለፍ ሲባል በቴክኖሎጂ የተደገፈ ስራ በመስራት ሂደቱን ግልጽና አሳታፊ ለማድረግ የተደረገው ተነሳሽነትና ጥረት እንዲሁም የባልሙያዎችን ሙያዊ ነፃነት አክብረን አስፈላጊውን ሂደት ተከትለን ተዓማኒነቱን እንዲያረጋግጡልን አድርገን ነበር:: በዚህ ሂደት በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮ አዲስ ሶፍትዌር እንዲበለፅግ እና ስለሶፍትዌሩ ታአማኒነት የኢኖቬንና ቴክኖሎጂ ሚንስቴር እንዲያረጋግጥልንም ተደርጓል::
በቀጣይም ከሁለት ጊዜ በላይ ታዛቢወች እና ባለሙያወች ፊት ቀርቦ እንዲያረጋግጡልን ተደርጎ ማረጋገጫ ሰጥተዋል::
ይህ ሁሉ ሂደት ከእለት ጉርሱ የቆጠበዉን እና በከፍተኛ ጉጉት የሚጠባበቀውን ሕዝብ በፍትሃዊነት ተደራሽ ለማድረግ ቀና ሃሳብ እንደሆነ መገንዘብ ይቻላል::
ይሁን እንጂ ከዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት በኋላ የተለያዩ ጥቆማዎች በመቅረባቸው የኦዲት ሥራ ስንጀምር በባንክ የተላከውና ለእጣ እንዲውል ወደ ኮምፒዩተር የተጫነው ዳታ ልዩነቶች ተግኝተዋል::
በመሆኑም በእስካሁኑ የማጠራት ስራ ላልቆጠቡ ሰዎች እጣ መውጣትን ጨምሮ የተለያዩ የተዓማኒነት ጉድለቶች ታይተዋል፡፡

ከዚህ በመነሳትም የቤት ማስተላለፉን ሂደት ግልፅነት ለማስፈን ሲባል እና ውጤቱን የሚያዛባ ተግባር ሲያጋጥም መልሰን ኦዲት እንዲደረግ በገባነው ቃል መሰረት የተፈጠረውን ችግር ከጉዳዩ ገለልተኛ በሆኑ በሚመለከታቸው ተቋማት የማጣራት ስራ በመከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን በጉዳዩ የተጠረጠሩ ባለሙያዎች እና አመራር በቁጥጥር ሥር ሆነው ምርመራ እየተደረገ ይገኛል::

ስለሆነም ሂደቱን በአጭር ጊዜ አጠናቀን ለቤት ተመዝጋቢዎችና ለመላው የከተማችን ነዋሪ የምናሳውቅ መሆኑን ስንገለጽ ተመዝጋቢዎች እንደተለመደው በከፍተኛ ትዕግስት እንድትጠባበቁ እናሳውቃለን፡፡

ለተፈጠረው ስህተት የከተማ አስተዳደሩ በዚህ አጋጣሚ ይቅርታ ይጠይቃል
አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
ሐምሌ 4/2014 ዓ/ም
3.7K views19:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 13:32:42
3.1K views10:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 13:32:30 ባለሶስት መኝታ ቆጣቢዎች በልዩ ሁኔታ እንዲስተናገዱ ተወሰነ

የ20/80 ባለሶስት መኝታ የጋራ መኖርያ ቤት እጣ አለመውጣትን አስመልክቶ ከከተማ አስተዳደሩ የተሰጠ ማብራርያ!

እንደሚታወቀው የከተማ አስተዳደሩ ባሳለፍነው ሳምንት የ20/80 የ14ኛ ዙር የ40/60 3ኛ ዙር የጋራ መኖርያ ቤት እጣ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡
ይህንን ተከትሎ በ20/80 ፕሮግራም የባለሶስት መኝታ ቤት ተመዝጋቢዎች በእጣው አለመካተትን መነሻ በማድረግ ከአንዳንድ ግለሰቦች የደረሰንን የግልፅነት ጥያቄ አስመልክቶ የሚከተለውን ማብራርያ ለማቅረብ እንወዳለን፡-

በዚህ ዙር ለ20/80 የቤት ፕሮግራም ሙሉ ለሙሉ እጣ የወጣባቸውና የተስተናገዱት የ1997 ተመዛጋቢዎች ብቻ ናቸው፡፡
የ2005 የ20/80 ተመዝጋቢዎች ግን ከስቱዲዮ ጀምሮ ባለአንድ ባለሁለትና ባለሶስት መኝታ በሙሉ በእጣ ውስጥ አልተካተቱም፡፡

የ40/60 የቤት ፕሮግራም ግን በ2005 ዓ.ም ብቁ የሆኑ ሙሉ ለሙሉ በእጣ ተካተው በዚህ ዙር የእጣ አወጣጥ በ40/60 ባለአንድ ባለሁለትና ባለሶስት መኝታ ቤቶች እጣ እንደወጣላቸው ልብ ሊባል ይገባል፡፡

ስለሆነም በዚህ ዙር ያልተስተናገዱት 1997 ዓ.ም የተመዘገቡ ባለሶስት መኝታ ተመዝጋቢዎች ብቻ ናቸው፡፡

ይህም የሆነበት ዋነኛ ምክንያት በ12ኛ ዙር እጣ የ1997 ባለሶስት መኝታ ተመዝጋቢዎችን ሙሉ ለሙሉ አስተናግደናል በሚል መነሻ መረጃቸው የተሟላ የሆኑት ተስተናግደው የባለሶስት መኝታ ፕሮግራም ተዘግቶ ነበር፡፡

ከዚህ በኋላ በ1997 ተመዝጋቢዎች ውስጥ በ20/80 ባለሶስት መኝታ እጣ ሊወጣለት የሚችል ተመዝጋቢ የለም በሚል ቤቶቹን በሚያስተዳድረው ቦርድ ውሳኔ ፕሮግራሙ ከሲስተም ውጪ እንዲሆን ተደርጓል።
በዚህም ምክንያት በዚህኛው(በ14ኛ) ዙር እጣ ማስተናገድ አልተቻለም::
ነገር ግን ከተዘጋ በኋላ ከባንክ የተገኘው መረጃ ጥቂቶች ቢሆኑም ቁጠባ በመቀጠላቸው ብቁ የሆኑ ጥቂቶች ተገኝተዋል::
በአሁን ሰአትም ምዝገባው ከባንክ በሚወሰድበት (በሚከለስበት ወቅት) በተገኘው መረጃ ከ1997 ተመዝጋቢዎች መሃከል ጥቂት ሰዎች በአግባቡ እየቆጠቡ ያሉና ብቁ የሆኑ የ20/80 ተመዝጋቢዎችን ማግኘት ተችሏል፡፡

ስለሆነም አስተዳደሩ እነኚህን ተመዝጋቢዎች ምንም እንኳን ፕሮግራሙ በይፋ የተዘጋ ቢሆንም ከባንክ በተገኘው መረጃ መሰረት በአግባቡ እስከቆጠቡ ድረስ ማስተናገድ እንደሚገባ ያምናል፡፡

ነገር ግን ከመረጃ ውስንነትና በሲስተሙ ላይ የሚያስከትለውን ተጨማሪ የመረጃ መመሰቃቀል ለመከላከል ሲባል ወደ በኋላ ተመልሶ ሲስተሙን ለቀሩት ጥቂት ቆጣቢዎች ብቻ መክፈት አስፈላጊ ሆኖ ባለመገኘቱ ምክንያት እነዚህን ተመዝጋቢዎች ለብቻቸው በልዩ ሁኔታ ልናስተናግድ ይገባል የሚል ውሳኔ ላይ ተደርሷል፡፡

ስለሆነም የ1997 ተመዝጋቢ ሆናችሁ ባለሶስት መኝታ ቤቶች በአግባቡ የቆጠባችሁ አስተዳደሩ በሚያወጣው ፕሮግራም በልዩ ሁኔታ የምትስተናገዱ መሆኑን እያሳወቅን ፤ ህብረተሰቡ ይህንን አስመልክቶ አንዳንድ የሚናፈሱ የተሳሳቱ መረጃዎች ራሱን እንዲጠብቅ ለማሳሰብ እንወዳለን!!
በተጨማሪም ዘርፉን የሚመሩ አመራሮች ተጨማሪ መረጃዎችን በተለያዩ ሚድያዎች የሚያደርሱ መሆኑንም እናሳውቃለን!!
3.5K views10:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 23:02:15
3.2K views20:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 09:33:13
3.7K views06:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 09:29:16 #EthiopiaCheck Monitoring

የ20/80 ባለ ሶስት መኝታ ቤት ተመዝጋቢዎች በዛሬዉ እጣ ያልተካተቱት ለምንድን ነዉ?

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሲያስገነባቸው የቆየዉን የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች እጣ የማዉጣት ስነስርዓት ዛሬ አካሂዷል።

ይሁን እንጂ በ20/80 ፕሮግራም ባለ ሶስት መኝታ ቤት የ1997 ተመዝጋቢዎች በእጣዉ ያለመካተት በርካቶች ዘንድ ብዥታን የፈጠረ መሆኑን ተመልክተናል። በርካታ የኢትዮጵያ ቼክ ተከታዮችም ስለጉዳዩ መረጃ ጠይቃችሁናል።

ኢትዮጵያ ቼክ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ፌስቡክ ገጽ መረዳት እንደቻለዉ በዛሬዉ እለት እጣ ከወጣባቸዉ 25491 ቤቶች ዉስጥ 18648ቱ የ20/80 ፕሮግራም ቤቶች ናቸዉ። እነዚህ 18648 ቤቶች ደግሞ ስቱድዮ፤ ባለአንድ መኝታ ቤት እና ባለሁለት መኝታ ቤት ናቸዉ።

ስለዚህም ባለ ሶስት መኝታ ቤት የ1997 ተመዝጋቢዎች በእጣዉ አልተካተቱም ማለት ነዉ።

የከተማ አስተዳደሩ “የባለ ሶስት መኝታ ቤት በተመለከተ ፕሮግራሙ ባለፈዉ ዙር በቦርድ ዉሳኔ በመዘጋቱ በቀጣይ በልዩ ሁኔታ የሚስተናገዱ ይሆናል” ሲል በፌስቡክ ገጹ ጽፏል።

የአዲስ አበባ ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሽመልስ ታምራት የ1997 20/80 ተመዝጋቢዎች በ12ኝዉ ዙር እጣ መመሪያዉ ከሚጠይቀዉ የ60 ወር ቁጠባ ወርዶ 1500 ብር የቆጠቡት ጭምር በእጣ መካተታቸዉን ለሚዲያዎች በሰጡት ማብራሪያ ተናግረዋል።

“በ12ኛ ዙር ላይ ቦርዱ መመሪያ አስተላልፎ፤ ቃለጉባኤ ይዞ፤ ወስኖ እስከ 1500 ድረስ ወርዶ ፈቀደላቸዉ። ከዛ በኋላ ‘የመጨረሻ እስከ 1500 ወርደናል ባለ ሶስት መኝታ አልቋል’ በሚል አናዉንስ ተደረገ” ብለዋል።

ይሁን እንጂ የ20/80 ፕሮግራም ቢዘጋም ጥቂት ሰዎች የባንክ ቁጠባ አካዉንታቸዉን ሳይዘጉ መቆጠብ መቀጠላቸዉን አቶ ሽመልስ ተናግረዋል።

በዛሬዉ የእጣ ስነስርዓት ያልተካተቱትም እነዚህ 20/80 ተመዝጋቢዎች ሲሆኑ ለወደፊት በሌላ መንገድ እንደሚስተናገዱም ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

“አሁን አጠቃላይ ነገሩን ከምናበላሸዉና ሲስተሙንም እንደገና ከምንደበላልቀዉ ጥቂት ስለሆኑ በዚህ እጣ ዉስጥ አይካተቱ ነገር ግን ከባንክ በወሰድነዉ መረጃ መሰረት እስከ የካቲት 21 (2014) ቆጥበዉ ብቁ የሆኑትን በሌላ መንገድ እናስተናግዳቸዋለን” ብለዋል።

ፎቶ: የከንቲባ ፅ/ቤት
3.8K views06:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ