Get Mystery Box with random crypto!

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ዩክሬን እንዲጎበኙ ከፕሬዝዳንቱ ግብዣ ቀረበላቸው፡፡ ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ | Ethio Fm 107.8

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ዩክሬን እንዲጎበኙ ከፕሬዝዳንቱ ግብዣ ቀረበላቸው፡፡

ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ ዩክሬንን እንዲጎበኙ ግብዣ ማድረጋቸው ተሰምቷል፡፡

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ ከዩክሬን ፕሬዝዳንት ዘለንኪ ጋር በስልክ ከተወያዩ በኃላ ነው ዩክሬን እንዲጎበኙ ጥሪ የተደረገላቸው ተብሏል፡፡

ከሩሲያ ጋር ጦርነት ውስጥ ያለችው ዩክሬን፣ለኢትዮጵያ 300 ሺህ ቶን ስንዴ ማቅረቧ የተሰማ ሲሆን፣ከሰሞኑ በጥቁር ባህር በኩል ለዓለም ሃገራት ስንዴ ለማቅረብ የነበረው ስምምነት ሩስያ ከሰሞኑ ከስምምነቱ መውጣቷ ይታወሳል፡፡

ኬቭን እንዲጎበኙ የተጋበዙት ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ግብዣውን ስለመቀበላቸው እስካሁን የተባለ ነገር የለም።

ከሩሲያ ጋር ጦርነት ውስጥ ያለችው ዩክሬን በጦርነት ውስጥም ሆና ለኢትዮጵያ 300 ሺህ ቶን ስንዴ አቅርባለች ተብሏል።

ከዚህ በተጨማሪም ዩክሬን ተጨማሪ 90 ሺህ ቶን ስንዴ ለኢትዮጵያ እንደምታቀርብ በዘገባው ላይ ተጠቅሷል።

በሔኖክ ወ/ገብርኤል

ሐምሌ 14 ቀን 2015 ዓ.ም

ለታማኝና ወቅታዊ መረጃዎች ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

YouTube

https://www.youtube.com/.../UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos