Get Mystery Box with random crypto!

ከፍተኛ ነዳጅ አምራች ከሆኑ ሀገራት አንዷ የሆነችዉ ናይጄርያ ነዳጅ አጥሮኛል እያለች ነው፡፡ በአ | Ethio Fm 107.8

ከፍተኛ ነዳጅ አምራች ከሆኑ ሀገራት አንዷ የሆነችዉ ናይጄርያ ነዳጅ አጥሮኛል እያለች ነው፡፡

በአለም አቀፍ ደረጃ የነዳጅ ዋጋ መናሩን ተከትሎ ናጄርያዊያን ባለሀብቶች ፊታቸውን ወደ ጸሕይ ብርሀን ማዞራቸውን አልጀዚራ ዘስነብቧል፡፡

ናይጄርያ ለ200ሚሊየን ዜጎቿ ከ12ሺህ ሜጋ ዋት የማይበልጥ የሀይል አቅርቦት እንዳላት ነው የሚነገረው፡፡
ይሕ በመሆኑ የተነሳም የሀገሪቱ ባለሀብቶች ፊታቸውን ሙሉ በሙሉ ወደ ጸሀይ ሀይል እንዳዞሩ ተሰምቷል፡፡

የናይጄርያ የነዳጅት ኮሚሽን እንዳስታወቀው ሀገሪቷ በአመት ለነዳጅ 22 ቢሊዮን ዶላር ፈሰስ ታደርጋለች፡፡
አሁን ባለው መረጃ መሰረት በናይጄርያ አንድ ሊትር ናፍጣ 800 ናይራ ወይም 1.93 የአሜሪካ ዶላር እየተሸጠ ይገኛል፡፡
ይህም ከዩክሬን ጦርነት ጋር ቀጥተኛ ግኑኝነት እንዳለው መረጃዉ አመልክቷል፡፡

በሔኖክ ወ/ገብርኤል
ሐምሌ 06 ቀን 2014 ዓ.ም