የካፍ ፕሬዝዳንት አዲስ አበባ ገብተዋል:: የካፍ ፕሬዝዳንት ፓትሪስ መትሴፔ ለአንድ ቀን የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ መግባታቸውን ካፍ ኦንላይን ጽፏል፡፡ በቆይታቸው ከፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ፣ ከባህል እና ስፖርት ሚኒስትሩ ቀጄላ መርዳሳ ፣ ከእግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ ጂራ እና ስፖርቱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ይገናኛሉ፡፡ ሞትሴፔ ከእግር ኳስ ክለቦች ፕሬዝደንቶች ጋር በመወያየት ጉብኝታቸውን እንደሚያጠናቅቁም ተገልጿል፡፡ በአቤል ጀቤሳ ሐምሌ 06 ቀን 2014 ዓ.ም 3.7K views09:13