ከቀኖናና ከህግ ውጪ በተደረገው ሲመት ከተሾሙት መካከል አባ ዘጋዘአብ አዱኛ በዚህ ሰዓት ቤተክርስቲያንን ይቅርታ ለመጠየቅ ቅደለስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት ተገኝተው ለብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የይቅርታ ደብዳቤ አስገብተዋል።
በደብዳቤአቸውም ያሳደገቻቸውን ፣ያስተማረቻቸውንና ለዚህ ክብር ያበቃቻቸውን ቤተክርስቲያን ማሳዘናቸውን ገልጸው ቅዱስ ሲኖዶስ ይቅርታ እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል።
የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ