ከንቲባ አዳነች አቤቤ የተናገሩ ፦
- አሁንም ማንኛውም ችግር ቢያጋጥም በፍጥነት እናርማለን፤ በኦዲት ጭምር እናረጋግጣለን።
- በ20/80 93,352 በ40/60 54,540 በድምሩ 146,892 ከባንክ በተገኘው መረጃ መሰረት እንዲጣራ ተደርጎ ወደ ሲስተሙ ገብቷል። በዚህም ብቁ እና ንቁ ተብለው ለዕጣው ተዘጋጅተዋል።
(ከንቲባዋ በንግግራቸው በድምር ሲሉ የገለፁት ቁጥር (93,352 + 54,540) 146,892 አጠቃላይ ድምሩ የሚመጣው 147,892 ነው ፤ ይህ ትላንትም በከተማው የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ተገልጾ የነበር ሲሆን ለምን ይህ ሊሆን እንደቻለ የሚመለከታቸውን አካላት ለመጠየቅ እንጥራለን።)
- በ1997 ተመዝጋቢ የነበሩ ባለ 3 መኝታ ቤት ተመዝጋቢዎች ቁጥራቸው እጅግ አነስተኛ በመሆኑ ባለፈው ከዕጣ አወጣጡ ውጭ ተደርገው ነበር ፤ በዚህም በቀረበው ቅሬታ ከ2005 ቆጣቢዎች ጋር ዛሬ ለዕጣ ብቁ እንዲሆኑ ተደርገዋል።
- ዛሬ ለዕጣ የተዘጋጁት 25,791 ቤቶች ከ1997 ብቁ እና ንቁ ተመዝጋቢዎችን ሙሉ በሙሉ በመያዝ ለዕጣው መውጣት ዝግጅቱ የተደረጉ ናቸው።
- ከዚህ በኃላ በ1997 የሚጠራ ብቁ እና ንቁ ተብለው የሚጠሩ ዕጣ የሚወጣላቸው የተለየ ሁኔታ ሳያስፈልግ ሙሉ ተመዝጋቢዎች ዛሬ ይስተናገዳሉ።