Get Mystery Box with random crypto!

ETHIO NEWS

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_news1 — ETHIO NEWS E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_news1 — ETHIO NEWS
የሰርጥ አድራሻ: @ethio_news1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8.01K
የሰርጥ መግለጫ

✍ በየእለቱ ትኩስ እና አዳዲስ የሀገር ውስጥ የአለም ዜናዎችን በፍጥነት ሰብስበን ወደናንተ እናደርሳለን ዘመናዊ በሆነ የመረጃ አሰጣጣችን ይረካሉ
ለእውነተኛ ለትክክለኛ መረጃ ብቻ እንሰራለን። ✍

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-11-19 00:58:57
ላልተወሰነ ጊዜ የውጭ ምንዛሪ የማይፈቀድላቸው ከውጭ የሚገቡ ዕቃዎች ዝርዝር ላይ ማሻሻያ ተደረገ

ላልተወሰነ ጊዜ የውጭ ምንዛሪ የማይፈቀድላቸው ከውጭ የሚገቡ ዕቃዎች ዝርዝር ላይ ማሻሻያ  መደረጉን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ላልተወሰነ ጊዜ ተላልፎ በነበረው የውጭ ምንዛሪ የማይፈቀድላቸው ከውጭ የሚገቡ እቃዎች ዝርዝር ላይ ማሻሻያ ማድረግ በማስፈለጉ ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ዕቃዎች ላይ ማሻሻያ ማድረጉን ሚኒስቴሩ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክና ለጉምሩክ ኮሚሽን በጻፈው ደብዳቤ አሳውቋል፡፡

ማሻሻያ የተደረገባቸው ከውጭ የሚገቡ ዕቃዎች የሚከተሉት ናቸው፦

1. በታሪፍ ቁጥር 9401. 9000 እና 9403. 9000 የሚመደቡ እቃዎች ክፍሎች ማምረቻ ግብአቶች፣

2. ምርቶቻቸውንና አገልግሎቶቻቸውን በውጭ ምንዛሬ የመሸጥ ፍቃድ ያላቸው ሬስቶራንቶችና ሱፐር ማርኬቶች የራሳቸውን የውጭ ምንዛሬ ተጠቅመው የሚያስገቧቸው ዕቃዎች፣

3. ባለ ኮከብ ሆቴሎች የራሳቸውን የውጭ ምንዛሬ ተጠቅመው የሚያስመጧቸው ዕቃዎችና

4. የቀረጥ ነጻ ሱቆች የሚያስመጧቸው ዕቃዎች

የውጭ ምንዛሬ ክልከላው እንደማይመለከታቸው ሚኒስቴሩ አመልክቷል፡፡
ላልተወሰነ ጊዜ የውጭ ምንዛሬ የማይፈቀድላቸው ከውጭ የሚገቡ የ38 እቃዎች ዝርዝር በጥቅምት ወር  2015 ዓ.ም ይፋ መደረጉ የሚታወስ ነው።
562 views21:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-17 08:23:26 Emailing Addis Lissan Hidar 8-2015 .pdf
609 views05:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-15 22:52:57 ETHIO NEWS አጠቃላይ_20_80_ነባር_ቤት_ፕሮግራም_አሸናፊዎች_ዝርዝር_xls_min_1_1.pdf
1.2K viewsedited  19:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-15 22:51:57 ETHIO NEWS አጠቃላይ_40_60_ቤት_ፕሮግራም_አሸናፊዎች_ዝርዝር_xls_min_1_3.pdf
1.2K viewsedited  19:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-15 18:37:49
የ14ኛ ዙር የ20/80 እና የ3ኛ ዙር የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ
.
በዛሬዉ ዕለት 14ኛዉ ዙር የ20/80 እና 3ኛ ዙር 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች የዕጣ ማውጣት ሥነ ስርዓት በአዲስአበባ ከተማ መስተዳድር ለባለእድለኞች ወጥቷል።

በዚህም 20/80 ነባር ተመዝጋቢዎች የ18 ሺሕ 630 ቤቶች ዕጣ፣ የ20/80 አዲስ ተመዝጋቢዎች ዕጣ ከ318 ቤቶች ውስጥ የ300 ተመዝጋቢዎች ዕጣ እንዲሁም የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ተመዝጋቢዎች የ6 ሺሕ 834 ቤቶች ዕጣ ወጥቷል።

የ20/80 አዲስ ተመዝጋቢዎች ዕጣ 18 የስቱዲዮ ቤቶች ሆነው ቆጣቢ የሌላቸው መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን ለጊዜው ቤቶቹ ለማንም በዕጣ እንደማይተላለፉ ተነግሯል።

በዕጣ ማውጣት ሥነ ስርዓቱ ላይም የመንግስት ሰራተኞች 20 በመቶ፣ ሴቶች 30 በመቶ፣ አካል ጉዳተኞች 5 በመቶ እንዲሁም ቀሪው 45 በመቶ በእጣ ባለእድለኞች እንደተለዩ ተገልጿል።

በተጨማሪም በባለሶስት መኝታ 300 መቶ ቤቶችን ቀሪ ሥራ በማከናወን ለነባርና አዲሰ ተመዝጋበዎች በዕጣ መካተታቸው ተነግሯል።

በዚህ ዕጣ የ20/80 ከ96 በመቶ በላይ፣ በ40/60 ከ87 በመቶ በላይ የግንባታ አፈጻጸም ያላቸው ቤቶችን ለዕጣ መቅረባቸውም ተገልጿል፡፡
1.3K views15:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-15 18:34:16
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የተናገሩ ፦

- አሁንም ማንኛውም ችግር ቢያጋጥም በፍጥነት እናርማለን፤ በኦዲት ጭምር እናረጋግጣለን።

- በ20/80 93,352 በ40/60 54,540 በድምሩ 146,892 ከባንክ በተገኘው መረጃ መሰረት እንዲጣራ ተደርጎ ወደ ሲስተሙ ገብቷል። በዚህም ብቁ እና ንቁ ተብለው ለዕጣው ተዘጋጅተዋል።

(ከንቲባዋ በንግግራቸው በድምር ሲሉ የገለፁት ቁጥር (93,352 + 54,540) 146,892 አጠቃላይ ድምሩ የሚመጣው 147,892 ነው ፤ ይህ ትላንትም በከተማው የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ተገልጾ የነበር ሲሆን ለምን ይህ ሊሆን እንደቻለ የሚመለከታቸውን አካላት ለመጠየቅ እንጥራለን።)

- በ1997 ተመዝጋቢ የነበሩ ባለ 3 መኝታ ቤት ተመዝጋቢዎች ቁጥራቸው እጅግ አነስተኛ በመሆኑ ባለፈው ከዕጣ አወጣጡ ውጭ ተደርገው ነበር ፤ በዚህም በቀረበው ቅሬታ ከ2005 ቆጣቢዎች ጋር ዛሬ ለዕጣ ብቁ እንዲሆኑ ተደርገዋል።

- ዛሬ ለዕጣ የተዘጋጁት 25,791 ቤቶች ከ1997 ብቁ እና ንቁ ተመዝጋቢዎችን ሙሉ በሙሉ በመያዝ ለዕጣው መውጣት ዝግጅቱ የተደረጉ ናቸው።

- ከዚህ በኃላ በ1997 የሚጠራ ብቁ እና ንቁ ተብለው የሚጠሩ ዕጣ የሚወጣላቸው የተለየ ሁኔታ ሳያስፈልግ ሙሉ ተመዝጋቢዎች ዛሬ ይስተናገዳሉ።
1.2K views15:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-14 22:48:50
የተሰረዘው የአዲስ አበባ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ነገ ከሰዓት ላይ የሚካሄደው የእጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓቱም በቴሌቪዠን #በቀጥታ_ስርጭት ይተላለፋል።

** 25 ሺህ 791 የ40/60 እና 20/80 ቤቶች ዕጣ ይወጣባቸዋል።

** በእጣ 146 ሺህ 892 እስከ የካቲት 21 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ በቂ ቁጠባ ያላቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ይሳተፋሉ።

** ነባርና በ2005 ዓ.ም በባለ 3 መኝታ ቤት የተሰሩ 300 ቤቶችም ይተላለፋሉ

** በእጣው ብቁ የሚሆኑት የ20/80 (ስቱዲዮ፣ ባለ 1 እና ባለ 2) ነባር ተመዝጋቢዎች (1997) ዝቅተኛውን የ60 ወራት ቁጠባ መጠን እንዲሁም የባለ 3 መኝታ ነባርና አዲስ ተመዝጋቢዎች (2005) ዝቅተኛውን የ84 ወራት ቁጠባ መጠን ያሟሉ መሆን ይገባቸዋል

** የ40/60 ተመዝጋቢዎች ከ40% እና ከዚያ በላይ ቁጠባ ያላቸው ለእጣ ውድድር ብቁ የሆኑ እስከ የካቲት 21/2014 ዓ.ም ድረስ መሰረት 40% የቆጠቡ።

** በ20/80 የቤት ልማት ፕሮግራም 93,352 እና በ40/60 የቤት ልማት ፕሮግራም 53,540 በአጠቃላይ 146,892 ተመዝጋቢዎች ለዕጣ ብቁ ሆነው በመገኘታቸው በዚህ ዙር ዕጣ ተካትው የቤት እድለኛ ለመሆን የሚወዳደሩ ይሆናል።

https://t.me/Ethio_news1
https://t.me/Ethio_news1
1.5K views19:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-12 21:56:34
#Peace

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ምን አሉ ?

የፕሪቶሪያ ስምምነትና የዛሬው ናይሮቢ ስምምነት ተፈፃሚ እንዲሆን ለማድረግ በሙሉ ቁርጠኝነት እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል።

ጀነራል ታደሰ ወረደ ምን አሉ ?

የዛሬው ስምምነት በትግራይ ውስጥ በህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን ስቃይ ያስወግዳል የሚል ተስፋ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።

ኡሁሩ ኬንያታ ምን አሉ ?

ኡሁሩ ኬንያታ በዛሬው መግለጫ ስምምነቱ በጦር ወንጀሎች ላይ " ተጠያቂነትን " ያጠቃልል እንደሆነ ለተጠየቀ ጥያቄ ምላሽ ሰጥተው ነበር።

ኡሁሩ ኬንያታ ይህ " የመሳሪያ ድምፅ ፀጥ ሲል እና አስከፊው የሰብአዊ ሁኔታ ሲስተካከል " እንደሚመጣ ተናግረዋል።

" በሰላማዊ ሰዎች ላይ ግፍ የሚፈጽም አካል ላይ ከባድ ማዕቀብ ይጣልበታል " ብለዋል።
354 views18:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-02 01:00:49 https://vm.tiktok.com/ZMFD89AFB/
135 views22:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-28 18:07:55
የተወዳጁና ድምጸ መረዋው አርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ የቀብር ሥነ ስርዓት ነገ ሐሙስ መስከረም 19 ቀን 2015 በአዲስ አበባ አራት ኪሎ መንበረ ጸባኦት ቅድስተ ሥላሴ ካቴድራል ቤተክርስትያን እንደሚፈጸም የቀብር አስፈጻሚ ኮሚቴው አስታወቀ።

የተወዳጁን የኪነጥበብ ሰው ሥርዓተ ቀብር ለማስፈጸም የተቋቋመው ኮሚቴ ጉዳዩን አስመልክቶ በአርቲስቱ በመኖሪያ ቤት ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥቷል።

አርቲስት አረጋኸኝ ወራሽ፥ የወንድማችን ህልፈት ድንገተኛ በመሆኑ ሀዘናችን መሪር ነው፥ በዚህ ሁኔታ መግለጫ መስጠትም ከባድ ነው ብሏል።

አርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅን በአጭር መግለጽ ከባድ ነው፤ በህይወት ዘመኑ የሰራቸው ተግባራት ግን ትውልድ የሚማርባቸው ይሆናሉ ሲል ገልጿል።

በነገው ዕለት የአስከሬን ስንብት በመኖሪያ ቤቱ በማድረግ በወዳጅነት ፓርክም ከ6፡ 00 ሰዓት ጀምሮ በመንግስት ኃላፊዎች፣ በሙያ አጋሮቹ፣ በአድናቂዎቹና ወዳጅ ዘመዶቹ የአስክሬን ስንብት እንደሚካሄድ ገልጿል።

በመቀጠልም ከቀኑ 10:00 ጀምሮ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴደራል ቤተክርስቲያን ስርዓተ ቀብሩ እንደሚፈጸም ተናግሯል።

ጎልማሳው የጥበብ ሰው ማዲንጎ አፈወርቅ ስለ ፍቅር፣ ትዝታ፣ ባህል፣ ሀገር፣ ታሪክና ሌሎች ጉዳዮችን የሚዳስሱ መልዕክቶችን በተስረቅራቂ ድምጹ በማዜም በኢትዮጵያ የኪነጥበብ ስራ ላይ የራሱን አሻራ አሳርፏል።

ድምጻዊ ማዲንጎ አፈወርቅ ኢትዮጵያ በተፈተነችበት ወቅት እያመመው ግንባር ድረስ በመሄድና ማሰልጠኛም ምልምሎችን በማነቃቃት የራሱ የሆነ ታሪክ የሰራ አርቲስት መሆኑም ይታወቃል።

በቀድሞው የጎንደር ክፍለ ሀገር አዘዞ ተወልዶ በደብረታቦር ያደገው አርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ መስከረም 17/2015 ዓ.ም ህይወቱ ማለፉ ይታወሳል።
441 views15:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ