2022-08-31 20:43:57
#ቂሷ
ክፍል-3
አብዱል ቀድር ጀይላኒ #ቂሷ
አብዱል ቀድር ጀይላኒ በጣም ትልቅ ሸይኽ እና ወልይ ነበሩ።እናታቸውም ጥሩ እና ሀቀኛ ሰው ነበረች። አብዱል ቀድር ጀይላኒን በህፃንነታቸው እናታቸው ሁለየ የምትመክራቸው ምክር ነበረ።
እሱም ምክር አደራህን ሰውን እንዳትዋሽ የሚል ነበር።
ከእለታት አንድ ቀን ወደ ደረስነት ለመላክ አሰበችና ከነጋዴወች ጋር አብራ ላከቻቸው።
ስተልካቸውም በዛ ያለ ገንዘብ ሰጣቸው ነበር።
እናም ከነጋዴወች ጋር አብረው መሄድ ጀመሩ እየሄዱም እያለ የሆነ መንገድ ላይ ሲደርሱ ሽፍቶች አጋጠሞቸው እነዛ ሽፍቶች እንዲህ አሏቸው የያዛችሁት ብር ስንት እንደሆነ ተናገሩ አሏቸው።
ያሁላ ነጋዴም ካላቸው እየቀነሱ ይሄን ታክል ነው ያለኝ ይሄን ታክልነው ያለኝ እያሉ ተናገሩ።
አብዱል ቀድር ጀይላኒን አንተ ህፃን ስንት ነው የያስከው ተናገር ሲላቸው አብዱል ቀድር ጀይላኒም ያላቸውን ምንም ሳያስቀሩ ተናገሩ ሲናገሩ ሽፍቶቹ ሳቁና እየ ቀለድክ ነው ይሄን ታክል ብር እንዴት ይኖርሀል ብለው ሁሎችንም እየፈተሹ ሲቀበሉ
የአብዱል ቀድር ጀይላኒን ብር ሲቆጥሩ ልክ እንዳለው ሁኖ አገኙት የሽፍቶች መሪም በመገረም እንዲህ አለው እንዴት እንደምንቀማህ እያወክ እውነቱን ለምን ተናገርክ ሲሏቸው እናቴ እንዳትዋሽ ስላለችኝ ነው አለ።
ያ የሽፍቶች መሪም በልቡ እንዲህ ብሎ አሰበ ይሄ ህፃን የናቱን ትዛዝ ምንም ሳያመነታ ሲወጣ እኔ ግን የፈጣሪየን የአሏህን ትእዛዝ ክጄ የሰውን ሀቅ እዘርፋለሁ አለ። ከእንግዲህ በኋላ የሰውን ሀቅ ላልወስድ ቃል እገባለሁ አለና የቀማቸውን ገንዘብ መልሶላቸው ከአብዱል ቀድር ጀይለኒ ጋር አብረው ወደ ደረስነት ሄዱ።
ከዚ ቂሷ ምን እንረዳለን
1 እውነትን በመናገር እራስን ማዳንና ለሰወች መቅናት ሰበብ መሆንን እንማራሐን
@Eslmnachin99 @Eslmnachin99
131 views __ابن محمد__ , 17:43