2022-08-25 21:07:53
#እባካችሁ ፀሎት ስትመሩ እነዚህን ንግግሮች ተጠንቀቁ
በቤተ-ክርስቲያንም ሆነ ብዙ ምዕመን በተሰበሰበበት ሌላ ቦታ
ፀሎት የመምራት ዕድል ስታገኙ በፀሎት ምሪታችሁ መካከል እነዚህን ሃሳቦች ባታነሱ መልካም ነው
"እጅ፡ እግር፡ አይን፡ ጆሮ…ወዘተ ስለሰጠን እያመሰገንን እንፀልያለን" አይባልም
እንዲህ አይነት ርዕስ በግል የፀሎት ጊዜያችን ሲሆን ችግር የለውም።
ነገር ግን ብዙ አይነት ሰው በተሰበሰበበት ቦታ ሆነን ፀሎት እየመራን ከሆን ችግር ይፈጥራል
ምክንያቱም በዚያ ጉባኤ መካከል ወይ እጅ ወይ እግር የሌለው ወይ ማየት ወይም መስማት የተሳነው አማኝ ሊኖር ይችላል።
"ብዙዎች እንደ ወጡ ሲቀሩ እኛ ግን በዚህ ስለተገኘን እናመስግን" አይባልም
አንተ ፀሎት በምትመራበት ጉባኤ መካከል ምናልባት
እናቱን ወይ አባቱን ወይ ጓደኛውን በድንገተኛ አደጋ ያጣ ሰው ሊኖር ይችላል።
ስለዚህ ያ ሰው እግዚአብሔር ለኛ መልካም ሆኖ ለሱ ክፉ እንደሆነ አድርጎ ሊረዳ ይችላል
"ብዙዎች በዚህ ሰዓት መንቀሳቀስ አቅቷቸው ሆስፒታል ተኝተዋል፡ እኛ ግን በዚህ እንድንገኝ እግዚአብሔር ረድቶናል" አይባልም
እናቱን ሆስፒታል አስተኝቶ የመጣ ሰው በጉባኤው መካከል ካለ ምን ይሰማው ይሆን?
እግዚአብሔር እኛን ወዶ እሱንና እናቱን እንደሚጠላ አድርጎ ሊረዳም ይችላል
እነዚህን ፀሎቶች በግል ጊዜአችን መፀለይ ክፋት የለውም።
የጉባኤ ፀሎት እየመራን ከሆነ ግን
በተቻለን መጠን የቆመውን፣ የወደቀውን
ጤነኛውን፡ በሽተኛውን
አንካሳውን፣ ሚራመደውን
ማየት የሚችለውን፡ ማየት የማይችለው፡ የሞተውን፡ ያልሞተውን
ሁሉንም አንድ አድርጎ ያቀፈውን #ክርስቶስን እየሰበክን በተሰጠን ዕድል
የወደቀውን እናንሳ! የደከመውን እናበርታ!
ለታመመው እንፀልይ!
ተስፋ ለቆረጠው ተስፋ እንስጥ!
እባክዎ መልዕክቱን share በማድረግ ለሌሎች ክርስቲያኖችም ያድርሱ
Share share share share
ቤተሰባችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/joinchat/VriY4W6tg1Yg7kqh
@berbantefeta
2.7K viewsT€Me$g£n A €G@, edited 18:07