በአሜሪካ ኢምባሲ የትምህርት ጉዳዮች አማካሪ የሆኑት አቶ ተክለሚካኤል ተፈራ ተቋማቸው በተለይ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎችን የማማከርና የመደገፍ አገልገሎት በስፋትና በጥልቀት ተጠናክሮ እንዲሰጥ ለማስቻል ለሚመለከታቸው አካላት የሚሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠና ዘዴን በተመለከተ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላትን መልምሎ ወደ ማዕከል በመጥራት፥ በቀጥታ በበይነመረብ በማግኝት፥ የተለያዩ ግብኣቶችን በመስጠት እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ የስልጠናው ይዘት ሳይንሳዊ እውነታንና የሀገራት ተሞክሮዎችን መሰረት ያደረገ ሲሆን በመክፈቻውም ወቅት አሜርካን ኢምባሲ 560 የተለያዩ የእንግልዝኛ ቋንቋ ማዳበሪያ መጽሃፍትን ለትምህርት ሚኒስቴር አበርክቷል፡፡ 3.3K views12:19