Get Mystery Box with random crypto!

' የተቀመጠው አድራሻ በአግባቡ ስለማይሰራ ውጤታችንን ማየት አልቻልንም ' - ተማሪዎች እና የተማሪ | ኢትዮ መረጃ University

" የተቀመጠው አድራሻ በአግባቡ ስለማይሰራ ውጤታችንን ማየት አልቻልንም " - ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የዘንድሮው የስምንተኛ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ መደረጉን አሳውቋል።

ቢሮው ተማሪዎች ውጤታቸውን https://aaceb.gov.et/%e1%8b%a88%e1%8a%9b-%e1%8a%ad%e1%8d%8d%e1%88%8d-%e1%8b%89%e1%8c%a4%e1%89%b5/ ወይም aaceb.gov.et ላይ በመግባት ማየት እንደሚችሉ ገልጾ ነበር።

ነገር ግን ቢሮው ይፋ ያደረገው ውጤት መመልከቻ አድራሻ በትክክል ስለማይሰራ ውጤት ለማየት እንዳልቻሉ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች አሳውቀዋል።

በመሆኑም ፤ የከተማው ትምህርት ቢሮ አድራሻው ላይ ያለውን ችግር እንዲያርም /እንዲያስተካክል እንዲሁም ለህዝብ ይፋ ከመደረጉ በፊት ተገቢውን ፍተሻ ማለፉን ሊያረጋግጥ ይገባል ብለዋል።

በአዲስ አበባ ከሰኔ 27 እስከ ሰኔ 29 /2014 ዓ/ም በተሰጠው የ8ኛ ክፍል ፈተና ከ71 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል።

በአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ይፋ በተደረገው መረጃ ለፈተናው ከተቀመጡ ተማሪዎች መካከል 63.9 ፐርሰንት ተማሪዎች 50 እና በላይ ውጤት አስመዝግበዋል፤ 85.5% ተማሪዎች ወደቀጣይ ክፍል ለመዛወር ችለዋል።